🔇Unmute
ሆሳዕና ፤ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተቋቋሙ የግብይት ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተረጋጋ የገበያ ስርዓት እየፈጠሩ መሆኑን አምራቾችና ሸማቾች ገለፁ።
በክልሉ ዱራሜና ወራቤ ከተሞች ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ሸማቾችና አምራቾች በክልሉ የተቋቁሙ የግብይት ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተረጋጋ የግብይት ስርዓት እየፈጠሩ ነው ብለዋል፡፡
አስተያየታቸውን ከሰጡ ሸማቾች መካከል የዱራሜ ከተማ ነዋሪው ወንድሙ ዋጠሮ በከተማው የተቋቋሙ የግብይት ማዕከላት ሳምንቱን ሙሉ የግብርናና የፋብሪካ ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ይህም የተረጋጋ ግብይትን በመፍጠር የነጋዴውንም ሆነ የሸማቹን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ መሆኑም አክለዋል።

በከተማው በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማሩት ካሰች አዎ በበኩላቸው የከተማው የግብይት ማዕከላት የእንስሳት ተዋፅኦዎችን በተመጣጣኝ ዋጋና በቅርበት ለሸማቹ እንዲያቀርቡ ማስቻላቸውን ገልጸዋል።
ይህም ምርታቸው ሳይበለሽ በጊዜና የማጓጓዟ ወጪያቸውን በቀነሰ መንገድ ሳምንቱን ሙሉ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከስደት መልስ በጥምር ግብርና ተደራጅታ ስራ መጀመሯን የገለጸችው መኪያ ጀማል በበኩሏ በከተማው የተገነባው ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከል የግብርና ምርታቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጻለች።
ከዚህ ቀደም ምርቶቻቸውን ወደ ተለያዩ አካባቢዎች ቦታዎች በማጓጓዝ ለገበያ ለማቅረብ የሚፈጅን ግዜና ተጨማሪ የትራንስፖርት ወጪ መቀነስ እንደቻለች አስታውሳለች፡፡
የግብይት ማዕከሉ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት በህገወጥ ነጋዴዎችና ደላሎች አማካኝነት በምርት ላይ የሚደረገውን ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ማስቀረቱን ገልፃለች።

የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ባዬሽ ተስፋዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው በክልሉ የህብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ ያማከለ አገልግሎት የሚሰጡ ግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ እየከተናወነ ነው ብለዋል፡፡
በክልሉ ከሚገኙ አጠቃላይ የግብይት ማዕከላት ውስጥ 102 የሚሆኑትን ሳምንቱን ሙሉ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል ማዕከላቱን የማዘመን ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
በግብይት ማዕከላቱ ሸማቹንና አምራቹን በማገናኘት በቅናሽ ዋጋ የግብርና፣ የፋብሪካና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ ነው ብለዋል፡፡
በዚህም የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው የኑሮ ውድነቱን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የግብይት ማዕከላትን የማጠናከር ስራ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራም ገልጸዋል።
ሆሳዕና ፤ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተቋቋሙ የግብይት ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተረጋጋ የገበያ ስርዓት እየ...
Jun 30, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ መሳካት፣ የባለድ...
Jun 26, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ፣ ከባሕር ጠለል በላይ በ1,910 ...
Jun 16, 2026
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026