የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት እየተጠናቀቁ ናቸው

Jun 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የህብረተሰቡን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማቀላጠፍና የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት እየተጠናቀቁ መሆኑ ተገለጸ።

በምስራቅ ወለጋ ዞን ዋዩ ቱቃ ወረዳ በ99 ሚሊየን ብር በላይ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

በፕሮጀክት ምረቃ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ለሜሳ አየለ እንደገለፁት፤ መንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍና የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው።


በዚህም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቁ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉት ፕሮጀክቶችም የስራ እድል የሚፈጥሩና የዞኑን የገቢ አቅም የሚያሳድጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የምስራቅ ወለጋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ደሱ ለሚ በበኩላቸው፤ መንግስት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ደረጃ በደረጃ ለመፍታት መስራቱን አንስተዋል።


ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናግረዋል።

ለአገልግሎት ክፍት ከተደረጉት ፕሮጀክቶች መካከል የስራ እድልን ማስፋት የሚያስችሉ የመስሪያና የመሸጫ ቦታዎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የምስራቅ ወለጋ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቃዱ ገመዳ በበኩላቸው፤ መንግስት ለህብረተሰቡ የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የገባውን ቃል ለመፈጸም በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


በዚህም እየተከናወኑ ባሉ ስራዎች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቁመው ለዚህም የዛሬዎቹ ፕሮጀክቶች ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የዋዩ ቱቃ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አማኑኤል መኮንን በበኩላቸው ፤ከ99 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የከብት እርባታ ማእከል ፣ ድልድዮች ፣ መንገዶች ፣ የቡሳ ጎኖፋ እህል ማከማቻ መጋዘን እና ሌሎች ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን ገልጸዋል።


የልማት ፕሮጀክቶቹም ለማህበረሰቡ ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡና የወረዳውን ማህበረሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንደሚያሳልጡ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026