የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ በግንባታ ላይ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ የካቲት 4/2017 (ኢዜአ)---የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች እየተገነቡ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

የተጎበኙት የመንገድ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በክልሉና በፌዴራል መንግስት ወጪ የሚገነቡ መንገዶች ናቸው።

በአመራሮቹ ከተጎበኙ መንገዶች ውስጥ ከሀዌላ ቱላ- ውጅግራ-ያዬ- ወራንቻ የሚገነባውና 85 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የአስፓልት መንገድ አንዱ ነው።

መንገዱ ሦስት ዞኖችን እርስ በርስ የሲዳማ ክልልን ከኦሮሚያ ክልል እንደሚያገናኝ ተመላክቷል።


ሌሎች የመንገድ ግንባታ መሰረተ ልማቶችም ወረዳን ከወረዳና ከዞን የሚያገናኙ ሲሆን በከተሞችም እየተገነቡ ያሉ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የጉብኝቱ አካል መሆናቸው ታውቋል።

በጉብኝቱ ላይ ከርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በተጨማሪ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችም ተገኝተዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026