
ሀዋሳ፤ የካቲት 4/2017 (ኢዜአ)---የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች እየተገነቡ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ
የተጎበኙት የመንገድ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በክልሉና በፌዴራል መንግስት ወጪ የሚገነቡ መንገዶች ናቸው።
በአመራሮቹ ከተጎበኙ መንገዶች ውስጥ ከሀዌላ ቱላ- ውጅግራ-ያዬ- ወራንቻ የሚገነባውና 85 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የአስፓልት መንገድ አንዱ ነው።
መንገዱ ሦስት ዞኖችን እርስ በርስ የሲዳማ ክልልን ከኦሮሚያ ክልል እንደሚያገናኝ ተመላክቷል።

ሌሎች የመንገድ ግንባታ መሰረተ ልማቶችም ወረዳን ከወረዳና ከዞን የሚያገናኙ ሲሆን በከተሞችም እየተገነቡ ያሉ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የጉብኝቱ አካል መሆናቸው ታውቋል።
በጉብኝቱ ላይ ከርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በተጨማሪ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችም ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026