
አዲስ አበባ፤የካቲት 23/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል ከኢትዮጵያ ባለፈ ለአፍሪካ ንግድና ቱሪዝም ትልልቅ ዕድሎችን የሚከፍት መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በምረቃ ስነስርዓቱ ወቅት እንዳሉት፤አዲስ አበባ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን የሚያጎሉ ፕሮጀክቶችን ቀርጻ እውን እያደረገች ነው።
የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የነገዋ ሴቶች ተሃድሶና የልህቀት ማዕከል እንዲሁም ብርሃን ማየት የተሳናቸው ትምህርት ቤት ባለፈው አንድ ዓመት እውን የሆኑ ስኬታማ ፕሮጀክቶች ናቸው ብለዋል።
የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከልም የአዲስ አበባን ብሎም የአፍሪካን ተወዳዳሪነት ከፍ ወዳለ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑንም አብራርተዋል።
ማዕከሉ ከኢትዮጵያ ባለፈ ለአፍሪካ ትልልቅ እድሎችን የሚከፍት ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች፥ ለቀጣናዊ ንግድ ትስስር መጠናከር፣ ጎብኝዎችን ለመሳብ እንዲሁም ለገጽታ ግንባታ አወንታዊ ሚና አለው ብለዋል።
ማዕከሉ የቢዝነስ ውይይቶችና የስምምነት መርሃ ግብሮችን ለማካሄድ፣ ልዩ ልዩ ኤግዚቢሽኖችና ባህላዊ መድረኮችን በብቃት ለማስተናገድ የሚያስችል አቅም ያለው መሆኑንም አስረድተዋል።
ሀገራዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ ለተጀመረው ጉዞ የማዕከሉ እውን መሆን ዓይነተኛ ሚና እንደሚያበረክትም ነው ከንቲባ አዳነች የገለጹት።
በመሆኑም የፌዴራልና የከተማ አስተዳደሩ የልማት ድርጅቶች በማዕከሉ ያላቸውን ድርሻ በማሳደግና የተፈጠረውን ዕድል በመጠቀም ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር አለባቸው ብለዋል።
ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማሳለጥ ሰፋፊ የልማት ሥራዎች በማከናወን እና የፕሮክጀክቶችን አፈጻጸም በማሻሻል ላይ ትኩረት መደረጉንም አንስተዋል።
የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በድል በመሻገር በትጋትና በታማኝነት ሥራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል።
አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል 40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን በድምሩ እስከ 10 ሺህ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ሁለት ትላልቅ እና 8 መካከለኛ አዳራሾችን ያካተተ ነው።
ባለ 5 ኮከብ ሆቴል፣ሬስቶራንቶች፣መዝናኛና የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ በአንድ ጊዜ 2 ሺህ ተሽከርካሪ ማስተናገድ የሚችል የመኪና ማቆሚያን ጨምሮ በርካታ አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተመላክቷል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026