የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ማዕከሉ ከኢትዮጵያ ባለፈ ለአፍሪካ ንግድና ቱሪዝም ትልልቅ ዕድሎችን የሚከፍት ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 23/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል ከኢትዮጵያ ባለፈ ለአፍሪካ ንግድና ቱሪዝም ትልልቅ ዕድሎችን የሚከፍት መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።


አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በምረቃ ስነስርዓቱ ወቅት እንዳሉት፤አዲስ አበባ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን የሚያጎሉ ፕሮጀክቶችን ቀርጻ እውን እያደረገች ነው።


የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የነገዋ ሴቶች ተሃድሶና የልህቀት ማዕከል እንዲሁም ብርሃን ማየት የተሳናቸው ትምህርት ቤት ባለፈው አንድ ዓመት እውን የሆኑ ስኬታማ ፕሮጀክቶች ናቸው ብለዋል።


የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከልም የአዲስ አበባን ብሎም የአፍሪካን ተወዳዳሪነት ከፍ ወዳለ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑንም አብራርተዋል።


ማዕከሉ ከኢትዮጵያ ባለፈ ለአፍሪካ ትልልቅ እድሎችን የሚከፍት ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች፥ ለቀጣናዊ ንግድ ትስስር መጠናከር፣ ጎብኝዎችን ለመሳብ እንዲሁም ለገጽታ ግንባታ አወንታዊ ሚና አለው ብለዋል።


ማዕከሉ የቢዝነስ ውይይቶችና የስምምነት መርሃ ግብሮችን ለማካሄድ፣ ልዩ ልዩ ኤግዚቢሽኖችና ባህላዊ መድረኮችን በብቃት ለማስተናገድ የሚያስችል አቅም ያለው መሆኑንም አስረድተዋል።


ሀገራዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ ለተጀመረው ጉዞ የማዕከሉ እውን መሆን ዓይነተኛ ሚና እንደሚያበረክትም ነው ከንቲባ አዳነች የገለጹት።


በመሆኑም የፌዴራልና የከተማ አስተዳደሩ የልማት ድርጅቶች በማዕከሉ ያላቸውን ድርሻ በማሳደግና የተፈጠረውን ዕድል በመጠቀም ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር አለባቸው ብለዋል።


ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማሳለጥ ሰፋፊ የልማት ሥራዎች በማከናወን እና የፕሮክጀክቶችን አፈጻጸም በማሻሻል ላይ ትኩረት መደረጉንም አንስተዋል።


የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በድል በመሻገር በትጋትና በታማኝነት ሥራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል።


አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል 40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን በድምሩ እስከ 10 ሺህ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ሁለት ትላልቅ እና 8 መካከለኛ አዳራሾችን ያካተተ ነው።


ባለ 5 ኮከብ ሆቴል፣ሬስቶራንቶች፣መዝናኛና የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ በአንድ ጊዜ 2 ሺህ ተሽከርካሪ ማስተናገድ የሚችል የመኪና ማቆሚያን ጨምሮ በርካታ አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026