ጅማ፣ መጋቢት 01/2017 (ኢዜአ)፦ ከ699 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥረው ሶስተኛው የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በተገኙበት በጅማ ከተማ ይፋ ሆኗል።
ሚኒስትሯ በማስጀመሪያ መርሃ ግብር እንዳሉት ፕሮጀክቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችን ህይወታቸውን ያሻሽላል።
ለቀጣይ ሶስት ዓመታተ የሚተገበረው ፕሮጀክቱ በሀገሪቷ በተለያዩ ከተሞች ከ699 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል የሚያመቻችና ብዙዎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት የሚቀይር መሆኑን ገልጸዋል።
ባለፉት ዓመታት በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ዘላቂ የኑሮ ማሻሻያ ተተግብሮ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል።
ፕሮጀክቱ ከኮሪደር ልማት ጋር ተጣጥሞ እንደሚተገብር ገልፀው፤ ከተሞቻችን ውብ፤ ጽዱና አረንጓዴ ሆነው ለነዋሪዎቻቸው ምቹ እንዲሆኑ በትብብርና በቅንጅት የሚሰራ መሆኑን አንስተዋል።
የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በበኩላቸው ልማታዊ ሴፍትኔቱ ለከተማችን ውበት አጋዥ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ወገኖቻችን የስራ እድል በመፍጠር ሕይወታቸውን የሚለውጥ ነው ብለዋል።
ከዚህ በፊት የልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ተጠቃሚ የነበሩ ነዋሪዎች በበኩላቸው በቆይታቸው ሰርተው ካገኙት ገንዘብም ቆጥበው መለወጣቸውን ለአብነት አንስተዋል።
በዚህ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ከተለያዩ ክልሎች የተውጣጡ የ88 ከተሞች አመራሮች እና የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025