
አዲስ አበባ፤መጋቢት 2/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት እና የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር መዓዛ አበራ (ኢ/ር) እና የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝዳንት አብርሃም ደበበ (ዶ/ር) ናቸው።
የጋራ መግባቢያ ስምምነቱ ተቋማቱ በሰው ሀብት አቅም ግንባታ እና ልማት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የልማት መስኮች እና በጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸው ነው።
ስምምነቱ ድርጅቱ በጥራት ማረጋገጥ ዘርፍ የልዕቀን ማዕከል ለመሆን የያዘውን ለማሳካት የሚያስችላው ወሳኝ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።
መዓዛ አበራ (ኢ/ር) የጋራ ትብብርን የሚያጠናክሩ ስምምነቶች ስራን ውጤታማ እንደሚያደርጉ መግለጻቸውን ከድርጅቱ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026