የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ተቋማቱ በጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ

Mar 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 2/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት እና የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል።


ስምምነቱን የተፈራረሙት የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር መዓዛ አበራ (ኢ/ር) እና የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝዳንት አብርሃም ደበበ (ዶ/ር) ናቸው።


የጋራ መግባቢያ ስምምነቱ ተቋማቱ በሰው ሀብት አቅም ግንባታ እና ልማት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የልማት መስኮች እና በጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸው ነው።


ስምምነቱ ድርጅቱ በጥራት ማረጋገጥ ዘርፍ የልዕቀን ማዕከል ለመሆን የያዘውን ለማሳካት የሚያስችላው ወሳኝ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።


መዓዛ አበራ (ኢ/ር) የጋራ ትብብርን የሚያጠናክሩ ስምምነቶች ስራን ውጤታማ እንደሚያደርጉ መግለጻቸውን ከድርጅቱ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026