
አዲስ አበባ፤መጋቢት 2/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት እና የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር መዓዛ አበራ (ኢ/ር) እና የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝዳንት አብርሃም ደበበ (ዶ/ር) ናቸው።
የጋራ መግባቢያ ስምምነቱ ተቋማቱ በሰው ሀብት አቅም ግንባታ እና ልማት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የልማት መስኮች እና በጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸው ነው።
ስምምነቱ ድርጅቱ በጥራት ማረጋገጥ ዘርፍ የልዕቀን ማዕከል ለመሆን የያዘውን ለማሳካት የሚያስችላው ወሳኝ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።
መዓዛ አበራ (ኢ/ር) የጋራ ትብብርን የሚያጠናክሩ ስምምነቶች ስራን ውጤታማ እንደሚያደርጉ መግለጻቸውን ከድርጅቱ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026