
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን ስታርታፖች የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶቻቸውን ከፓን አፍሪካ የወጣቶች አመራር ጉባኤ ጎን ለጎን በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ላይ አስተዋውቀዋል።
ጉባኤው "የወጣቶችን አቅም - ለበለፀገች አፍሪካ" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል።
ጉባኤውን አስመልክቶ የተዘጋጀ ኤግዚቢሽንም ተከፍቷል።

በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ላይ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የፌዴራል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ሚኒስትሮች፣ የፓን አፍሪካ ወጣት አመራሮች እና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
በጉባኤው የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን ስታርታፖች የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶቻቸውን በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ላይ ማስተዋወቃቸውን ከሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026