
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 15/2017(ኢዜአ)፦ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ 4ኛው ክልላዊ የስራ ፈጠራ ውድድር መርሃ ግብርን አስጀምረዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ውድድሩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በቴክኒክ ሙያ ኮሌጆች መምህራን እና ተማሪዎች የሚዘጋጁ የፈጠራ ስራዎች የማህበረሰቡን የእለት ተእለት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚያቃልሉ ሊሆኑ ይገባል።
በውድድሩ 12 የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆች 34 መምህራን፣ 59 ተማሪዎች እና 2 የግል ድርጅቶች መቅረባቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

በተወዳዳሪዎቹ ተዘጋጅተው ከቀረቡ የፈጠራ ውጤቶች መካከል የእርሻ ምርት መሰብሰቢያ ማሽኖች፣ የዶሮ መፈልፈያ፣ የእንስሳት መኖ ማዘጋጃና ለቤት ግንባታ የሚውሉ ግብዓቶች እንደሚገኙበትም ተጠቁሟል።
ለውድድሩ የሚቀርቡ የፈጠራ ስራዎች የማህበረሰቡን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆን እንደሚገባቸው ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።
በውድድሩ ላይ ለእይታ የቀረቡ ምርቶች የክልሉን ህዝብ የእለት ተእለት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚያቃልሉና የወጣቶችን የስራ ፈጠራ ባህል የሚያበረታቱ እንዲሆኑም አስገንዝበዋል።
በፈጠራ ላይ የሚሰማሩ ሰዎች የሚሰሯቸውን ሥራዎች ለመደገፍ የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ጥረት እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።

የሶማሌ ክልል የክህሎትና ሥራ እድል ፈጠራ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሁሴን ጌይድ፤ 4ኛ ዙር ዓመታዊ የቴክኒክ ኮሌጆች ያቀረቡት ምርቶች ለግብርና፣ ለእንስሳት እርባታና ለስራ ፈጠራ የላቀ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱና አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች የቀረበበት ነው ብለዋል።
ለሶስት ቀናት የሚቆየው ይህ ውድድር "ጤናና አምራች ዜጋ ለሁለንተናዊ እድገት መሰረት ነው" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚቆይ ሲሆን በውድድሩ ለሚያሸንፉ ተወዳዳሪዎች እውቅና እና ሽልማት እንደሚበረክት ገልጸዋል።
በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ፣ የክልሉ የክህሎትና ስራ እድል ፈጠራ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሁሴን ጌይድ፤ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አደንና ሌሎች አመራሮች መገኘታቸው ተጠቅሷል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026