የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ 4ኛው ክልላዊ የስራ ፈጠራ ውድድር መርሃ ግብርን አስጀመሩ

Apr 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 15/2017(ኢዜአ)፦ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ 4ኛው ክልላዊ የስራ ፈጠራ ውድድር መርሃ ግብርን አስጀምረዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ውድድሩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በቴክኒክ ሙያ ኮሌጆች መምህራን እና ተማሪዎች የሚዘጋጁ የፈጠራ ስራዎች የማህበረሰቡን የእለት ተእለት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚያቃልሉ ሊሆኑ ይገባል።

በውድድሩ 12 የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆች 34 መምህራን፣ 59 ተማሪዎች እና 2 የግል ድርጅቶች መቅረባቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።


በተወዳዳሪዎቹ ተዘጋጅተው ከቀረቡ የፈጠራ ውጤቶች መካከል የእርሻ ምርት መሰብሰቢያ ማሽኖች፣ የዶሮ መፈልፈያ፣ የእንስሳት መኖ ማዘጋጃና ለቤት ግንባታ የሚውሉ ግብዓቶች እንደሚገኙበትም ተጠቁሟል።

ለውድድሩ የሚቀርቡ የፈጠራ ስራዎች የማህበረሰቡን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆን እንደሚገባቸው ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።

በውድድሩ ላይ ለእይታ የቀረቡ ምርቶች የክልሉን ህዝብ የእለት ተእለት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚያቃልሉና የወጣቶችን የስራ ፈጠራ ባህል የሚያበረታቱ እንዲሆኑም አስገንዝበዋል።

በፈጠራ ላይ የሚሰማሩ ሰዎች የሚሰሯቸውን ሥራዎች ለመደገፍ የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ጥረት እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።


የሶማሌ ክልል የክህሎትና ሥራ እድል ፈጠራ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሁሴን ጌይድ፤ 4ኛ ዙር ዓመታዊ የቴክኒክ ኮሌጆች ያቀረቡት ምርቶች ለግብርና፣ ለእንስሳት እርባታና ለስራ ፈጠራ የላቀ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱና አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች የቀረበበት ነው ብለዋል።

ለሶስት ቀናት የሚቆየው ይህ ውድድር "ጤናና አምራች ዜጋ ለሁለንተናዊ እድገት መሰረት ነው" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚቆይ ሲሆን በውድድሩ ለሚያሸንፉ ተወዳዳሪዎች እውቅና እና ሽልማት እንደሚበረክት ገልጸዋል።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ፣ የክልሉ የክህሎትና ስራ እድል ፈጠራ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሁሴን ጌይድ፤ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አደንና ሌሎች አመራሮች መገኘታቸው ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026