የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

5ኛው የፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ይካሄዳል

May 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ 5ኛው የፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ ከግንቦት 7 እስከ 9/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሸሪፍ ሚያን ገለጹ።

አምባሳደሩ በሰጡት መግለጫ፥ በንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕዩ ላይ ከ100 በላይ የፓኪስታን አምራች ድርጅቶች ይሳተፋሉ ብለዋል።

ከአፍሪካ ሀገራት ጋር የንግድ ትስስርን የሚያጠናክሩ የሕክምና መድኃኒት ምርትና መሣሪያዎች፣ የውበትና ቆዳ እንክብካቤ ውጤቶች፣ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ምርቶች፣ የምግብና የምግብ ነክ የግብርና ምርቶች፣ የአውቶሞቲቭ መለዋወጫዎች፣ የኤሌክትሪክና የቤት እቃዎች በአውደ ርዕዩ እንደሚቀርቡም ገልጸዋል።

በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር፥ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የፓኪስታን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ፈሰስ እንዲያደርጉ ተነሳሽነት እየፈጠረ ነው ብለዋል።

ባለሀብቶቹ በግብርና ማቀነባበር፣ በጨርቃጨርቅ፣ በሕክምና እና ሌሎች የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሳተፉ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

5ኛው የፓኪስታን አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ በኢትዮጵያና ፓኪስታን መካከል ያለውን ጠንካራ ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል።

በፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ የአፍሪካ ሀገራት እና የፓኪስታን መንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የንግድ መሪዎችና ባለሃብቶች የሚሳተፉ ሲሆን፥ ዝግጅቱም የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የንግድ ልማት ጉባኤ፣ የሁለትዮሽ የንግድ ውይይቶች፣ የመንግስት ለመንግስት የምክክር መድረኮችን ጨምሮ የተለያዩ ሁነቶች እንደሚካሄዱም ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025