አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ 5ኛው የፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ ከግንቦት 7 እስከ 9/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሸሪፍ ሚያን ገለጹ።
አምባሳደሩ በሰጡት መግለጫ፥ በንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕዩ ላይ ከ100 በላይ የፓኪስታን አምራች ድርጅቶች ይሳተፋሉ ብለዋል።
ከአፍሪካ ሀገራት ጋር የንግድ ትስስርን የሚያጠናክሩ የሕክምና መድኃኒት ምርትና መሣሪያዎች፣ የውበትና ቆዳ እንክብካቤ ውጤቶች፣ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ምርቶች፣ የምግብና የምግብ ነክ የግብርና ምርቶች፣ የአውቶሞቲቭ መለዋወጫዎች፣ የኤሌክትሪክና የቤት እቃዎች በአውደ ርዕዩ እንደሚቀርቡም ገልጸዋል።
በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር፥ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የፓኪስታን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ፈሰስ እንዲያደርጉ ተነሳሽነት እየፈጠረ ነው ብለዋል።
ባለሀብቶቹ በግብርና ማቀነባበር፣ በጨርቃጨርቅ፣ በሕክምና እና ሌሎች የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሳተፉ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
5ኛው የፓኪስታን አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ በኢትዮጵያና ፓኪስታን መካከል ያለውን ጠንካራ ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አንስተዋል።
በፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ የአፍሪካ ሀገራት እና የፓኪስታን መንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የንግድ መሪዎችና ባለሃብቶች የሚሳተፉ ሲሆን፥ ዝግጅቱም የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የንግድ ልማት ጉባኤ፣ የሁለትዮሽ የንግድ ውይይቶች፣ የመንግስት ለመንግስት የምክክር መድረኮችን ጨምሮ የተለያዩ ሁነቶች እንደሚካሄዱም ይጠበቃል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025