
አዲስ አበባ፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለኢንሹራንስ ዘርፉ አስተማማኝ መሰረት የሚጥል መሆኑን የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ፕሬዚዳንት ፓቲ መርቲን ገለጹ።
ፕሬዝዳንቷ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ እያደረገችው ያለውን የሪፎርም ስራ አድንቀዋል።
በተለይም በሀገር አቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የፋይናንስ ዘርፉን ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የወሰደቻቸው የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለውጥ በመፍጠር ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል።
ሀገሪቷ ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለመገንባት እያደረገችው ያለው ጥረት ለኢንሹራንስ ዘርፉ ዕድገትና ቀጣይነት መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል።
በአፍሪካ የኢንሹራንስ ዘርፉ በሚፈለገው ደረጃ ዕድገት ባያስመዘግብም ኢትዮጵያን ጨምሮ አንዳንድ ሀገራት በዘርፉ በትኩረት እየሰሩበት መሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።
የኢንሹራንስ ገበያውን ተደራሽነት ለማስፋትም የፋይናንስ ሥርዓቱን ማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው ነው ያብራሩት።
የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ዓለምን እየፈተኑ መሆኑን አንስተው፥ ለዚህ ደግሞ በቂ ምላሽ የሚሰጥና አደጋን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ የኢንሹራንስ ተቋማትን መገንባት ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከአስተናገደችው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ጉባኤ በተጓዳኝ ከተለያዩ የኢንሹራንስ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች ጋር በዘርፉ ስለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችላይ ውይይት ማድረጋቸውንም ፕሬዚዳንቷ አንስተዋል።
በቀጣይም በአፍሪካ የኢንሹራንስ ዘርፉ ለአጠቃላይ ምጣኔ ሃብታዊ ዕድገትና ለህዝቦች ተጠቃሚነት ሚናውን እንዲያሳድግ እንሰራለን ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026