የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለኢንሹራንስ ዘርፉ አስተማማኝ መሰረት ይጥላል-የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ፕሬዚዳንት

May 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለኢንሹራንስ ዘርፉ አስተማማኝ መሰረት የሚጥል መሆኑን የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ፕሬዚዳንት ፓቲ መርቲን ገለጹ።


ፕሬዝዳንቷ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ እያደረገችው ያለውን የሪፎርም ስራ አድንቀዋል።


በተለይም በሀገር አቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የፋይናንስ ዘርፉን ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የወሰደቻቸው የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለውጥ በመፍጠር ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል።


ሀገሪቷ ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለመገንባት እያደረገችው ያለው ጥረት ለኢንሹራንስ ዘርፉ ዕድገትና ቀጣይነት መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል።


በአፍሪካ የኢንሹራንስ ዘርፉ በሚፈለገው ደረጃ ዕድገት ባያስመዘግብም ኢትዮጵያን ጨምሮ አንዳንድ ሀገራት በዘርፉ በትኩረት እየሰሩበት መሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።


የኢንሹራንስ ገበያውን ተደራሽነት ለማስፋትም የፋይናንስ ሥርዓቱን ማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው ነው ያብራሩት።


የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ዓለምን እየፈተኑ መሆኑን አንስተው፥ ለዚህ ደግሞ በቂ ምላሽ የሚሰጥና አደጋን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ የኢንሹራንስ ተቋማትን መገንባት ይገባል ብለዋል።


ኢትዮጵያ ከአስተናገደችው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ጉባኤ በተጓዳኝ ከተለያዩ የኢንሹራንስ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች ጋር በዘርፉ ስለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችላይ ውይይት ማድረጋቸውንም ፕሬዚዳንቷ አንስተዋል።


በቀጣይም በአፍሪካ የኢንሹራንስ ዘርፉ ለአጠቃላይ ምጣኔ ሃብታዊ ዕድገትና ለህዝቦች ተጠቃሚነት ሚናውን እንዲያሳድግ እንሰራለን ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026