የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ ሦስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት እያለማች ነው - ኢንስቲትዩቱ

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቆይታ ጊዜዋና በመረጃ መሰብሰብ የተሻለ አቅም ያላትን ሦስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት እያለማች መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ኢትዮጵያ ETRSS-01 እና ET-Smart-RSS የተሰኙ ሁለት የመሬት ምልከታ ሳተላይቶችን ከቻይና የሳተላይት ማስወንጨፊያ ጣቢያ ወደ ሕዋ መላኳ ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ETRSS-02 የሚል ስያሜ የተሰጣትን ሦስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት በቅርቡ እንደምታመጥቅ መግለጻቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ ኢኒስቲትዩቱ የተለያዩ የሳተላይት መረጃዎችን በማደራጀትና በመተንተን ለሀገር ጥቅም እንዲውል እየሰራ ይገኛል።

በዚሁ መሰረት ሁለቱ ሳተላይቶች በተቀመጠላቸው ጊዜ የተሰጣቸውን ተልዕኮ ማሳካታቸውን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የገለጹት።


ከሳተላይቶቹ የተገኙት መረጃዎች ለግብርና፣ ለቱሪዝም፣ ለመሬት አስተዳደር፣ ለተፈጥሮ ሀብት፣ ለአደጋ ስጋት ቅነሳ አና ለሌሎች ስራዎች በግብዓትነት መዋላቸውን አመልክተዋል።

ተቋማትም የወሰዷቸውን መረጃዎች ጥናትና ምርምርን ጨምሮ ለተለያዩ ስራዎቻቸው እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ጨምረው ገልጸዋል።

ሦስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ከ12 እስከ 18 ወራት ባለ ጊዜ ውስጥ ለማምጠቅ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።

የሳተላይት ቁጥር መጨመር የመረጃ ግኝት እና ወቅታዊነቱም ጭምር እያደገ እንደሚሄድ አክለዋል።

በተለይም ሦስተኛዋ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ቀደም ሲል ከነበሩት የተሻለ አቅም ያላት፣ የቆይታ ጊዜዋም ከፍ ያለ እና የተሻለ መረጃ መስጠት የሚያስችል አቅም ያላት መሆኑን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026