
አፋር፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ) የአፋር ክልልን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆናቸውን የክልሉ ውሃ እና ኢነርጂ ቢሮ ገለፀ።
በአፋር ክልል ቂልበት ረሱ ዞን መጋሌ ወረዳ ገሚሪዳ ቀበሌ በ38 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።
በምረቃ ሰነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ አህመድ ሻሚ እንደገለፁት የክልሉን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ናቸው።

በዛሬው ዕለት የተመረቀው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትም ለህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ የሰጠና በክልሉ መንግስት እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑን አንስተዋል።
በፀሐይ ብርሃን ኃይል የሚንቀሳቀሰውና 38 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ፕሮጀክቱ ከ5 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ገልፀዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የዞኑ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ሐሰን በበኩላቸው በስፍራው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ማህበረሰቡ ላለፉት ዓመታት በንፁህ መጠጥ ውሃ እጦት ሳቢያ ሲያጋጥመው የነበረውን ችግር እንደሚፈታ ተናግረዋል።


በተለይም እናቶች የመጠጥ ውሃ ለማግኘት ከሚያደርጉት ረጅም ጉዞ እንግልትና በዚህም ምክንያት ሲባክን የነበረውን ጊዜ በመቆጠብ ረገድ እፎይታን የሰጠ ነው ብለዋል።
በምረቃ ስነ ሰርዓቱ ላይም የዞኑና የወረዳ የስራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026