
አፋር፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ) የአፋር ክልልን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆናቸውን የክልሉ ውሃ እና ኢነርጂ ቢሮ ገለፀ።
በአፋር ክልል ቂልበት ረሱ ዞን መጋሌ ወረዳ ገሚሪዳ ቀበሌ በ38 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።
በምረቃ ሰነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ አህመድ ሻሚ እንደገለፁት የክልሉን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ናቸው።

በዛሬው ዕለት የተመረቀው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትም ለህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ የሰጠና በክልሉ መንግስት እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑን አንስተዋል።
በፀሐይ ብርሃን ኃይል የሚንቀሳቀሰውና 38 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ፕሮጀክቱ ከ5 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ገልፀዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የዞኑ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ሐሰን በበኩላቸው በስፍራው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ማህበረሰቡ ላለፉት ዓመታት በንፁህ መጠጥ ውሃ እጦት ሳቢያ ሲያጋጥመው የነበረውን ችግር እንደሚፈታ ተናግረዋል።


በተለይም እናቶች የመጠጥ ውሃ ለማግኘት ከሚያደርጉት ረጅም ጉዞ እንግልትና በዚህም ምክንያት ሲባክን የነበረውን ጊዜ በመቆጠብ ረገድ እፎይታን የሰጠ ነው ብለዋል።
በምረቃ ስነ ሰርዓቱ ላይም የዞኑና የወረዳ የስራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026