
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፦ እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት ባለፉት ወራት 364ሺህ የንግድ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎትን በኦንላይን ማከናወኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አስታወቀ።
70ሺህ አዳዲስ የንግድ ፈቃዶችን በኦንላይን መስጠቱን ቢሮው ገልጿል።
የንግድ ቢሮው ምክትል ኃላፊ ፍስሀ ጥበቡ ለኢዜአ እንዳሉት፥ በበጀት ዓመቱ ለንግዱ ማህበረሰብ የሚሰጡ አገልግሎቶችን የሚያሳልጡ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ጥቅም ላይ ማዋል ተችሏል ብለዋል።
በወረዳና በክፍለ ከተማ በተበታተነ መልኩ የሚሰጠውን የንግድ ፈቃድ አገልግሎት በአንድ ማዕከል መስጠት የሚያስችል አደረጃጀት ለመፍጠር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት 411ሺህ የንግድ ፈቃድ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ በአሥር ወራት ብቻ 364ሺህ የንግድ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በኦንላይን መከናወኑን ተናግረዋል።
ከ70ሺህ የማያንሱ አዳዲስ የንግድ ፈቃድ ምዝገባ አገልግሎት በኦንላይን መሰጠቱንም ነው ጨምረው የገለጹት።
ህገ-ወጥና ኢ-መደበኛ የንግድ ስራዎችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር መልክ ለማስያዝ ስኬታማ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ከሚወሰዱ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎች ባሻገር በሁሉም ክፍለ ከተሞች ዘመናዊ የንግድ መስሪያ ቦታ በማዘጋጀት ወደ ህጋዊ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በኦንላይን ንግድ ፈቃድ ካደሱ ነጋዴዎች መካከል አቶ ፍስሃ ገብረመስቀል፥ ቀድም ሲል የነበረው የንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት አሰጣጥ ምቹ እንዳልነበር በማስታወስ፥ አሁን ሁሉም ነገር ቀላል መሆኑን ተናግረዋል።
የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ንግድ ፈቃዳቸውን ማሳደስ በመቻላቸው ጊዜያቸውን ከመቆጠብ ባለፈ እንግልት እንዳስቀረላቸው ጠቅሰዋል።
አዲስ የንግድ ፈቃድ ማውጣትም ሆነ የእድሳት አገልግሎትን በዘመናዊ መንገድ መጀመሩ ጊዜውን የዋጀ እና ለህብረተሰቡም ፋይዳው የላቀ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ ይርዳው ምትኩ ናቸው።
ሌላኛዋ አስተያያት ሰጪ ወይዘሮ መቅድስ ታደሰ፤ ቀድም ሲል ንግድ ፈቃድ ለማደስ ረጅም ጊዜ ይወስድ እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ላይ በኦንላይን መደረጉ ተጠቃሚ አድርጎኛል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026