
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፦ እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት ባለፉት ወራት 364ሺህ የንግድ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎትን በኦንላይን ማከናወኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አስታወቀ።
70ሺህ አዳዲስ የንግድ ፈቃዶችን በኦንላይን መስጠቱን ቢሮው ገልጿል።
የንግድ ቢሮው ምክትል ኃላፊ ፍስሀ ጥበቡ ለኢዜአ እንዳሉት፥ በበጀት ዓመቱ ለንግዱ ማህበረሰብ የሚሰጡ አገልግሎቶችን የሚያሳልጡ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ጥቅም ላይ ማዋል ተችሏል ብለዋል።
በወረዳና በክፍለ ከተማ በተበታተነ መልኩ የሚሰጠውን የንግድ ፈቃድ አገልግሎት በአንድ ማዕከል መስጠት የሚያስችል አደረጃጀት ለመፍጠር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት 411ሺህ የንግድ ፈቃድ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ በአሥር ወራት ብቻ 364ሺህ የንግድ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በኦንላይን መከናወኑን ተናግረዋል።
ከ70ሺህ የማያንሱ አዳዲስ የንግድ ፈቃድ ምዝገባ አገልግሎት በኦንላይን መሰጠቱንም ነው ጨምረው የገለጹት።
ህገ-ወጥና ኢ-መደበኛ የንግድ ስራዎችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር መልክ ለማስያዝ ስኬታማ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ከሚወሰዱ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎች ባሻገር በሁሉም ክፍለ ከተሞች ዘመናዊ የንግድ መስሪያ ቦታ በማዘጋጀት ወደ ህጋዊ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በኦንላይን ንግድ ፈቃድ ካደሱ ነጋዴዎች መካከል አቶ ፍስሃ ገብረመስቀል፥ ቀድም ሲል የነበረው የንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት አሰጣጥ ምቹ እንዳልነበር በማስታወስ፥ አሁን ሁሉም ነገር ቀላል መሆኑን ተናግረዋል።
የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ንግድ ፈቃዳቸውን ማሳደስ በመቻላቸው ጊዜያቸውን ከመቆጠብ ባለፈ እንግልት እንዳስቀረላቸው ጠቅሰዋል።
አዲስ የንግድ ፈቃድ ማውጣትም ሆነ የእድሳት አገልግሎትን በዘመናዊ መንገድ መጀመሩ ጊዜውን የዋጀ እና ለህብረተሰቡም ፋይዳው የላቀ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ ይርዳው ምትኩ ናቸው።
ሌላኛዋ አስተያያት ሰጪ ወይዘሮ መቅድስ ታደሰ፤ ቀድም ሲል ንግድ ፈቃድ ለማደስ ረጅም ጊዜ ይወስድ እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ላይ በኦንላይን መደረጉ ተጠቃሚ አድርጎኛል ብለዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026