
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በአሁኑ ወቅት 265 ሺህ ገደማ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሔደ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ መንግስት የመኖሪያ ቤት እጥረትን ለመፍታት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል።
የቤት ችግር ከፍተኛ ሥራ የሚፈልግ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መልኩ በመንግስት፣ በግል፣ በመንግስትና የግል ትብብር የመኖሪያ ቤቶቹ ግንባታዎች እየተካሄዱ መሆኑን አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅትም 265 ሺህ ገደማ የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን ጠቁመው፤ መንግስት ከግል ባለሃብቱ ጋር በቅንጅት በመስራት የሕዝቡን ፍላጎት ለማሟላት ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት አንድ ሚሊዮን ያህል ቤቶች መገንባታቸውን አውስተው፤ የመኖሪያ ቤቱ ግንባታ ደረጃውን የጠበቀና ለኑሮ ምቹ የሆነ በማድረግ ረገድ ሰፊ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ከመኖሪያ ቤት ግንባታው ጎን ለጎንም ከ100 ሺህ ያላነሱ የመኖሪያ ቤቶች በክረምት በጎ ፈቃድ ጥገና የሚደረግላቸው መሆኑንም ነው ያነሱት።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026