
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበለትን የ2018 ዓ.ም የፌደራል መንግስት በጀት አጽድቋል።
ምክር ቤቱ 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።
በስብሰባው ላይ የምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ የ2018 ዓ.ም የፌደራል መንግስት ረቂቅ በጀት የውሳኔ ሀሳብ እና ሪፖርት አቅርበዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሳኔ ሀሳቡን በመመርመር የ2018 የፌደራል መንግስት ረቂቅ በጀትን አፅድቋል።
በሪፖርቱ ላይ የቀጣይ በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት በጀት 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር መሆኑ ተመላክቷል።
ከ2018 ረቂቅ በጀት 1 ነጥብ 2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ እንዲሁም 14 ቢሊዮን ብር ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ የሚውል ነው።
ከረቂቅ በጀቱ 1 ትሪሊዮን ብር ወይም 73 በመቶውን ከታክስ ገቢ 236 ቢሊዮን ብር ከልማት አጋሮች ቀሪውን ደግሞ ከፕሮጀክቶች ድጋፍና ልዩ ልዩ ገቢዎች ለማግኘት ታቅዷል።
በረቂቅ በጀቱ ከጥቅል ሀገራዊ ምርት አንፃር ያልተጣራ የበጀት ጉድለት 2 ነጥብ 2 በመቶ እንዲሁም የተጣራ የበጀት ጉድለት 1 በመቶ መሆኑ በሪፖርቱ ላይ ተገልጿል።
መንግስት የበጀት ጉድለቱን በቀጥታ ከብሔራዊ ባንክ ብድር በመውሰድ ሳይሆን በግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ እንደሚሸፍንም ተጠቁሟል።
የ2018 ረቂቅ በጀት የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን እና የ10 ዓመቱን መሪ የልማት እቅድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ የተዘጋጀ እንደሆነም በሪፖርቱ ላይ ቀርቧል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026