
ሐይቅ ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ) ፡-በሐይቅ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት የማንሰራራት ጉዞ ሂደቱን የሚያጠናክር ነው ሲሉ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) አስታወቁ።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የክልልና የደቡብ ወሎ ዞን አመራሮች የሐይቅ ከተማ የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።

በዚህ ወቅት ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) ፤ ዛሬ በሐይቅ ከተማ የተመለከትነው የኮሪደር ልማት ጅምር ስራ የማንሰራራት ጉዞ ሂደቱን የሚያጠናክር ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ የከተማውን ገጽታ ይበልጥ ውብ በማደረግ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኚዎችና ለኢንቨስትመንት ምቹ ማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል።
የሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ መንገድና በገበታ ለትውልድ እየተገነባ ያለው የሐይቅ ሎጎ ፕሮጀክት የከተማዋን እድገት በማፋጠን የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።
መንግስት ከሕዝብ ጋር ተቀናጅቶ ኮሪደርን ጨምሮ ሌሎቸንም የልማት ተግባራት እያከናወነ በውጤታማነት በመቀጠል የብልፅግናን ጉዞ እያሳካ መሆኑን አስረድተዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን በበኩላቸው፤ በዞኑ ስር በሚገኙ ሶስት ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

የሐይቅ ከተማ የኮሪደር ልማት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማስፈፀም ተገቢው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የከተማውን የኮሪደር ልማት ሥራ እስከ ታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሐይቅ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር መሀመድ ናቸው።

ልማቱ የእግረኛና የብስክሌት መንገድን እንዲሁም አረንጓዴ ሥፍራና መዝናኛዎችንም ያካተተ ነው ብለዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026