
ጅማ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ) ፡- የአጋሮ የኮሪደር ልማት የከተማውን መልካም ገጽታ ከማጉላት ባለፈ ከተማዋን ለነዋሪዎችና ጎብኚዎች ይበልጥ ምቹ በማድረግ ለውጥ ማምጣቱ ተገለጸ።
የከተማው የኮሪደር ልማት 12 ነጥብ 4 ኪሎሜትር በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የከተማው አስተዳደር አስታውቋል።

ከአጋሮ ነዋሪዎች መካከል አቶ ሀፊዝ ከድር በሰጡት አስተያየት፤ የኮሪደር ልማቱ እግረኛና ተሽከርካሪ በተጨናነቀ ሁኔታ የሚጓዝበት የነበረውን ሂደት በመቀየር ይበልጥ ምቹ ማድረጉን ተናግረዋል።

ልማቱ የአጋሮን ከተማ መልካም ገጽታ በማጉላት ለነዋሪዎችና ጎብኚዎች ከቀድሞ በተሻለ ምቹ በመሆን ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል።
ሌላው የከተማዋ ነዋሪ መምህር ሲሳይ ማረጌ አጋሮ ፤ በኮሪደር ልማቱ መንገድን ከማስፋት ባሻገር የእግረኛ መንገድ መለየቱና አካፋይ መተላላፊያ ላይ የተተከሉት ችግኞች አረንጓዴን በማልበስ ጭምር የከተማዋን ውበት ይበልጥ ጎልቶ እንዲወጣ ማስቻሉን ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹና ማራኪ ከማድረጉ ባለፈ ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን የገለጹት ደግሞ አቶ ነቢል አሊ ናቸው።
የተተከሉ ሳሮች እና የተገነቡ ፋውንቴኖች ለአጋሮ ከተማ ልዩ ውበት መሆኑንና ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚደግፉ ተናግረዋል።

የአጋሮ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ነዚፍ መሀመድአሚን በበኩላቸው፤ የከተማው የኮሪደር ልማት 12 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ልማቱ የአረንጓዴ ልማት፣ ፋዎንቴኖችና ኮፊ ኮርነሮች የተካተቱበት ነው ያሉት ከንቲባው ከ10ሺ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የስራ እድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026