የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የተገነባልን የመስኖ መሰረተ ልማት ልማቱን በስፋት ለማከናወን ያግዘናል - አርሶ አደሮች

Jul 8, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ የተገነባልን የመስኖ መሰረተ ልማት ልማቱን በስፋት ለማከናወን ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኡራ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ በ74 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባ የፀንፀሀሎ የመስኖ መሠረተ ልማት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን በተገኙበት ተመርቋል።

የመስኖ ፕሮጀክቱ 200 ሄክታር ማሳ ማልማት የሚችልና ከ800 በላይ የሚሆኑ የሶስት ቀበሌ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የአካባቢው አርሶ አደሮች የመስኖ መሠረተ ልማቱ ከዚህ በፊት የሚያከናውኑትን የመስኖ ልማት ለማስፋፋት እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል።

አርሶ አደር ሙሀመድ ሙዘሚል እና ዳውድ አጣሂር ከዚህ በፊት በአነስተኛ የመስኖ ስራ ሲጠቀሙ ቢቆዩም ብዙም ውጤታማ እንዳልነበሩ ገልፀዋል።

አሁን ላይ የተጠናቀቀው የመስኖ መሰረተ ልማት ከፍተኛ ርዝመት ያለው የውሀ መውረጃ ቦይ ያለውና ውሀን በሁሉም አቅጣጫ ተደራሽ ማድረግ የሚችል በመሆኑ የመስኖ ልማቱን በስፋት ማከናወን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

ሌላው ወጣት አርሶ አደር አብዱ አልቃዲ በበኩሉ የመስኖ መሰረተ ልማት ግንባታው ከመደበኛ የግብርና ስራችን በተጨማሪ በመስኖ ልማት እንድንሳተፍ እና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዝ ነው ብሏል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ባበክር ሀሊፋ በበኩላቸው በክልሉ በዘንድሮው በጀት ዓመት የ11 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቁን ገልጸዋል።

አርሶ አደሩ በመስኖ ልማት ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸው የመስኖ መሰረተ ልማቱን በመጠቀም የበለጠ ምርታማ መሆን እንደሚቻል ተናግረዋል።

የፀንፀሀሎ መስኖ መሰረተ ልማት ሰፊ የማልማት አቅም ያለው በመሆኑ አርሶ አደሩ በኩታ ገጠም የተለያዩ የሰብል አይነቶችን በማምረት ተጠቃሚ እንደሚሆን አስታውቀዋል።

የመስኖ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ማህበረሰብ ተሳትፎ የላቀ እንደነበር የገለጹት ደግሞ ግንባታውን ያከናወነው ወርቅነህ ግዛው የውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ስራ አስኪያጅ ወርቅነህ ግዛው ናቸው።

የመስኖ ፕሮጀክቱ ለአሳ እርባታና ለሌሎች የግብርና ስራዎች ምቹ መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026