
ወላይታ ሶዶ ፤ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ)፡-የህዝብን ሁለንተናዊ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የገቢ አቅምን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አመለከተ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስትቲዩት ከባለድርሻ አካላት ቢሮዎች ጋር በመተባበር በክልሉ 11 ከተሞች ላይ የገቢ አቅምን በተመለከተ ባካሄደው ጥናት ዙሪያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ውይይት ተካሄዷል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ እና የአማካሪዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ቦሻ ቦምቤ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ያለውን የገቢ አቅም ለመለየት የሚያስችል ጥናት መካሄዱን ተናግረዋል።
በጥናቱ መሰረትም የክልሉን 75 በመቶ ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚያስችል አቅም መኖሩን መለየት መቻሉን ጠቅሰው ጥናቱ የገቢ አማራጮችንና የማደግ ተስፋን፣ ማነቆዎችንና መፍትሄዎችን ያመላከተ መሆኑንም ተናግረዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት የገቢ አቅም መጨመሩ የተመላከተ ቢሆንም በክልሉ የሚንቀሳቀሰው ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ያህል ገቢ እየተሰበሰበ አለመሆኑም ታይቷል ነው ያሉት።
በመሆኑም በጥናቱ የተገኘውን የመፍትሄ ሃሳብና ምልከታዎች ተግባራዊ በማድረግ የገቢ አማራጮችን አሟጦ በመጠቀም ክልሉ በራሱ ገቢ ወጪውን የሚሸፍንበትን እድል መፍጠር ይገባል ብለዋል።

የክልሉ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዮሐንስ በየነ፤ የክልሉን ህዝብ ሁለንተናዊ የልማት ጥያቄ ለመመለስ ይቻል ዘንድ የገቢን አቅም ማሳደግ ተገቢ መሆኑን አንስተዋል።
በዘርፉ የተለያዩ ማነቆዎች ቢኖሩም የገቢ መጠን እያደገ መምጣቱን ጠቁመው የመደበኛ እና ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢዎችን ይበልጥ ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት ማድረግ ይገባል ብለዋል።
በጥናቱ ያልታዩ የገቢ ምንጮችንም ጭምር በመቃኘት ገቢ የመሰብሰብ አቅምን በማሳደግ ልማትን ማስቀጠልና የህዝብን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በውይይቱ ላይም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት፣ የገቢዎች ቢሮ፣ የፋይናንስ ቢሮ፣ የፕላንና ልማት ቢሮ፣ የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ እና የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026