የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የህዝብን ሁለንተናዊ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የገቢ አቅምን ይበልጥ ማጠናከር ይገባል

Jul 8, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ ፤ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ)፡-የህዝብን ሁለንተናዊ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የገቢ አቅምን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አመለከተ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስትቲዩት ከባለድርሻ አካላት ቢሮዎች ጋር በመተባበር በክልሉ 11 ከተሞች ላይ የገቢ አቅምን በተመለከተ ባካሄደው ጥናት ዙሪያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ውይይት ተካሄዷል።


በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ እና የአማካሪዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ቦሻ ቦምቤ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ያለውን የገቢ አቅም ለመለየት የሚያስችል ጥናት መካሄዱን ተናግረዋል።

በጥናቱ መሰረትም የክልሉን 75 በመቶ ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን የሚያስችል አቅም መኖሩን መለየት መቻሉን ጠቅሰው ጥናቱ የገቢ አማራጮችንና የማደግ ተስፋን፣ ማነቆዎችንና መፍትሄዎችን ያመላከተ መሆኑንም ተናግረዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት የገቢ አቅም መጨመሩ የተመላከተ ቢሆንም በክልሉ የሚንቀሳቀሰው ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ያህል ገቢ እየተሰበሰበ አለመሆኑም ታይቷል ነው ያሉት።

በመሆኑም በጥናቱ የተገኘውን የመፍትሄ ሃሳብና ምልከታዎች ተግባራዊ በማድረግ የገቢ አማራጮችን አሟጦ በመጠቀም ክልሉ በራሱ ገቢ ወጪውን የሚሸፍንበትን እድል መፍጠር ይገባል ብለዋል።


የክልሉ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዮሐንስ በየነ፤ የክልሉን ህዝብ ሁለንተናዊ የልማት ጥያቄ ለመመለስ ይቻል ዘንድ የገቢን አቅም ማሳደግ ተገቢ መሆኑን አንስተዋል።

በዘርፉ የተለያዩ ማነቆዎች ቢኖሩም የገቢ መጠን እያደገ መምጣቱን ጠቁመው የመደበኛ እና ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢዎችን ይበልጥ ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት ማድረግ ይገባል ብለዋል።

በጥናቱ ያልታዩ የገቢ ምንጮችንም ጭምር በመቃኘት ገቢ የመሰብሰብ አቅምን በማሳደግ ልማትን ማስቀጠልና የህዝብን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

በውይይቱ ላይም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት፣ የገቢዎች ቢሮ፣ የፋይናንስ ቢሮ፣ የፕላንና ልማት ቢሮ፣ የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ እና የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026