የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በመዲናዋ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ366ሺህ ወጣቶች ቋሚ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል - ቢሮው

Jul 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ366 ሺህ ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል መፈጠሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማዋ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ አስተዳደሩ ባለፉት ዓመታት ለዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ሲሰራ ቆይቷል።

በ2017 በጀት ዓመት መጀመሪያ በአዲስ አበባ ለ300ሺህ ስራ ፈላጊዎች በፍትሃዊነት የስራ ዕድል ለመፍጠር ዕቅድ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰዋል፡፡

በዚህም ቢሮው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከሁለት ነጥብ አንድ ሚሊየን በላይ ከሆኑ ስራ ፈላጊ ወጣቶችና ወላጆች ጋር ውይይት ማድረጉንም ጠቅሰዋል።

ስራ ፈላጊዎችን በፍትሃዊነት ለመቀበል በተሰራው ስራ 403ሺህ ዜጎችን በኦን ላይን በመመዝገብ በበጀት ዓመቱ ለ366ሺህ 44 ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል በመፍጠር አፈጻጸሙን ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።

የስራ "ድል ከተፈጠረላቸው መካከል 55 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውም ጨምረው ተናግረዋል።

ለወጣቶቹ በከተማ ግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በንግድና ሌሎች ዘርፎች የስራ ዕድል በመፍጠር በቅጥርና በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የወጣቶች ሀገር እንደመሆኗ ይህንኑ ኃይል ወደ አምራችና አልሚነት መቀየር ተገቢ መሆኑን ነው የተናገሩት።

አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ከማድረግ ባሻገር ለስራ ፈላጊ ወጣቶች በርካታ የስራ ዕድሎች መፈጠራቸውን ጠቅሰው፤ ወጣቶች ዕድሉን በአግባቡ በመጠቀም ራሳቸውንና ሀገራቸውን በኢኮኖሚ ማበልጸግ እንደሚችሉ ገልጸዋል።

የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች በበኩላቸው፤ የተፈጠረላቸው የስራ ዕድል ራሳቸውን ለመለወጥ አቅም እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡


በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራው የባህሩና ጓደኛሞቹ ድርጅት ስራ አስኪያጅ ወጣት ባህሩ ፈየራ እድሉን ከማግኘቱ በፊት በተመረቀበት ሙያ ስራ ማግኘት ባለመቻሉ የቤተሰብ ጥገኛ እንደነበር አስታውሷል።

መንግስት ባመቻቸው ዕድል በመጠቀም የመስሪያ ሼድ እና የገንዘብ ብድር በማግኘቱ ቋሚ የስራ ዕድል ተፈጥሮለት ስራ በመጀመሩ ደስተኛ መሆኑን ተናግሯል።


ወጣት ሆኖ የሰራ ቅጥር ከመጠበቅ አማራጭ የስራ ዕድሎችን በአግባቡ በመጠቀም የተሻለ ገቢ ማግኘት ይቻላል ያለችው ደግም በከብት ማድለብ ስራ ላይ የተሰማራችው ወይዘሮ ስለእናት ታፈሰ ናት።


ወጣቶች በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ በተፈጠረው የስራ ዕድል መጠቀም አለባቸው ያለን ደግሞ የስራ ዕድል የተፈጠረለት ወጣት ዮናስ ደምሴ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026