
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ366 ሺህ ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል መፈጠሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማዋ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ አስተዳደሩ ባለፉት ዓመታት ለዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ሲሰራ ቆይቷል።
በ2017 በጀት ዓመት መጀመሪያ በአዲስ አበባ ለ300ሺህ ስራ ፈላጊዎች በፍትሃዊነት የስራ ዕድል ለመፍጠር ዕቅድ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰዋል፡፡
በዚህም ቢሮው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከሁለት ነጥብ አንድ ሚሊየን በላይ ከሆኑ ስራ ፈላጊ ወጣቶችና ወላጆች ጋር ውይይት ማድረጉንም ጠቅሰዋል።
ስራ ፈላጊዎችን በፍትሃዊነት ለመቀበል በተሰራው ስራ 403ሺህ ዜጎችን በኦን ላይን በመመዝገብ በበጀት ዓመቱ ለ366ሺህ 44 ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል በመፍጠር አፈጻጸሙን ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።
የስራ "ድል ከተፈጠረላቸው መካከል 55 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውም ጨምረው ተናግረዋል።
ለወጣቶቹ በከተማ ግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በንግድና ሌሎች ዘርፎች የስራ ዕድል በመፍጠር በቅጥርና በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ የወጣቶች ሀገር እንደመሆኗ ይህንኑ ኃይል ወደ አምራችና አልሚነት መቀየር ተገቢ መሆኑን ነው የተናገሩት።
አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ከማድረግ ባሻገር ለስራ ፈላጊ ወጣቶች በርካታ የስራ ዕድሎች መፈጠራቸውን ጠቅሰው፤ ወጣቶች ዕድሉን በአግባቡ በመጠቀም ራሳቸውንና ሀገራቸውን በኢኮኖሚ ማበልጸግ እንደሚችሉ ገልጸዋል።
የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች በበኩላቸው፤ የተፈጠረላቸው የስራ ዕድል ራሳቸውን ለመለወጥ አቅም እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡

በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራው የባህሩና ጓደኛሞቹ ድርጅት ስራ አስኪያጅ ወጣት ባህሩ ፈየራ እድሉን ከማግኘቱ በፊት በተመረቀበት ሙያ ስራ ማግኘት ባለመቻሉ የቤተሰብ ጥገኛ እንደነበር አስታውሷል።
መንግስት ባመቻቸው ዕድል በመጠቀም የመስሪያ ሼድ እና የገንዘብ ብድር በማግኘቱ ቋሚ የስራ ዕድል ተፈጥሮለት ስራ በመጀመሩ ደስተኛ መሆኑን ተናግሯል።

ወጣት ሆኖ የሰራ ቅጥር ከመጠበቅ አማራጭ የስራ ዕድሎችን በአግባቡ በመጠቀም የተሻለ ገቢ ማግኘት ይቻላል ያለችው ደግም በከብት ማድለብ ስራ ላይ የተሰማራችው ወይዘሮ ስለእናት ታፈሰ ናት።

ወጣቶች በሀገር ሰርቶ ለመለወጥ በተፈጠረው የስራ ዕድል መጠቀም አለባቸው ያለን ደግሞ የስራ ዕድል የተፈጠረለት ወጣት ዮናስ ደምሴ ነው፡፡
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026