
ነገሌ ቦረና፤ ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ)፡- በምስራቅ ቦረና ዞን ከ4 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ ዛሬ በነገሌ ቦረና ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፡፡

በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱረዛቅ ሁሴን እንደገለጹት፤ ለአገልግሎት ከበቁት ውስጥ የመጠጥ ውሀ፣ የጤና፣ የትምህርትና የመንገድ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል።
የመንግስት ድጋፍና የሕዝቡ ተሳትፎን ጨምሮ የተገነቡት እነዚህ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገባቸው አስታውቀዋል።
ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸው የሕብረተሰቡን የመሰረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄን ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት የተደረገው ጥረት አካል እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡
ለፕሮጀክቶቹ ግንባታ መሳካት ሕዝቡ ፣ የፌዴራልና የክልሉ መንግስት ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ ፤ የክልሉ መንግስት የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እንዳስገነባ ገልጸዋል፡፡
በምስራቅ ቦረና ዞን የተገነቡት ችግር ፈቺ ፕሮጀክቶች የግንባታ አፈጻጸም ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ብለዋል፡፡
መንግስት የአርብቶ አደሩን ፍትሀዊ የልማት ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ የጀመረው ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የዞኑ ሕዝብ የአካባቢውን ሰላምንና የተገነቡ ፕሮጀክቶች በመጠበቅና በመንከባከብ የድርሻውን እንዲወጣም መልዕከት አስተላልፈዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026