የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ፎረሙ ምርቶቻችንን ያስተዋወቅንበትና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ልምድ ያገኘንበት ነው - አምራቾች

Jul 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ ሶስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም የገበያ ትስስር ለመፍጠርና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ የሚያስችል ልምድ እንዲያገኙ ማስቻሉን በፎረሙ በተከፈተው ኤግዚቢሽን የተሳተፉ አምራቾች ገለፁ።

ላለፉት ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ዛሬ ተጠናቋል።

የማጠቃለያ መርሃ ግብሩም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ሚኒስትሮች፣ ሥራ ፈጣሪዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ተካሂዷል።

በፎረሙ ላይ ምርቶቻቸውን ይዘው የቀረቡ በማምርቻው ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች እንዳሉት ፎረሙ የገበያ ትስስር የፈጠሩበትና የተሻለ ልምድ ያገኙበት ነው።

ከአምራቾቹ መካከል የቆዳ ውጤቶች ማምረት ሥራ ላይ የተሰማሩት ሶስና ሲሳይ፥ ከዚህ ቀደም የቆዳ ውጤቶችን ገዝተው ሲሸጡ መቆያተቸውን አውስተዋል።

ከሁለት ዓመት ወዲህ የቆዳ ምርቶችን በእጅ በመስራት ወደ ገበያ ማቅረብ የጀመሩ ሲሆን ከራሳቸው አልፎ ለስድስት ሰዎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ገልፀዋል።

ፎረሙ በዘርፉ የተሻለና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉበት ልምድ ማግኘታቸን ነው ያስረዱት።

ለሁለት አስርት ዓመታት የሚጠጋ ጊዜ ተቀጥረው ሲሰሩ የቆዩት ጌጤ አስፋው በበኩላቸው ለወትሮው ለራሳቸውና ለሚቀርቧቸው ሰዎች የሹራብ አልባሳትን በስጦታ መልክ ሰርተው ያቀርቡ እንደነበር ተናግረዋል።

አሁን ላይ ሶስት ሆነው በመደራጀት የጀመሩት ቢሊሌ የሹራብ አልባሳት ስራ አድጎ፥ ለአራት ሰዎች ቋሚ የስራ እድል መፍጠሩን ጠቁመዋል።

የአፍሪካ ሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም የገበያ ትስስር ከመፍጠር ባለፈ ልምድ እንዲለዋወጡና የላቀ መነሳሳትን እንዲፈጥሩ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል።

ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ባህላዊ አልባሳትን መስራት የጀመሩት የዕለት ገብረአብ፥ አሁን ላይ 5 የቤተሰብ አባላትን በሙያ አሰልጥነው ወደ ስራ ማስገባታቸውን ነው ያነሱት።

የተለያዩ አልባሳትና የደንብ ልብሶችን ላለፉት 9 ዓመታት በማምረት ለገበያ ሲያቀርብ የቆየው የሎዛ ጋርመንት ምክትል ስራ አስኪያጅ ገነት ጥላሁን በበኩላቸው፥ አሁን ላይ ከ20 በላይ ለሆኑ ሰዎች ቋሚ የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል።

ፎረሙ ምርቶቻቸውን የተሻለ ማድረግ የሚችሉበት ተሞክሮ ያገኙበትና የሀገር ውስጥ ምርትን ለማበረታታት አስተዋፅኦ እንዳለው ገልፀዋል።

አምራቾቹ በተለይም ወጣቶች ከጠባቂነት ይልቅ ስራ ፈጣሪ ለመሆን ፍላጎታቸውን መሰረት ያደረገ ስራ ላይ አተኩረው እንዲሰሩም መክረዋል።

አሁን ላይ ያለውን ሰፊ የስራ እድል በመጠቀም ስራ ፈጣሪ በመሆን ራን፣ ቤተሰብን እና ሀገርን ለመጥቀም ተግቶ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026