
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማን የመንገድ መሰረተ ልማት በሚፈለገው ደረጃ ለማሳደግ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ሰራተኞችና በየደረጃው የሚገኘው አመራር የበለጠ መትጋት እንዳለባቸው ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ2017 በጀት አመት በመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታው መስክ ለተገኘው ስኬት ለሰራተኞቹ የምስጋናና የእውቅና መርሃ-ግብር አካሂዷል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ከንቲባዋ እንደገለጹት የከተማዋ የመንገድ ሽፋን ገና ብዙ መስራትን የሚጠይቅ ነው።

በዚህ ሒደት የባለስልጣኑ ሰራተኞች አሁን ለተደረሰበት ደረጃ ያሳዩት ትጋትና የስራ ተነሳሽነት የሚያስመሰግናቸው እንደሆነ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
ከተማችን አለም አቀፍ ተወዳዳሪ እስከምትሆን ድረስ 24/7 ነው የምንሰራው ያሉት ከንቲባዋ ለሰራተኞቹ የተሰጠው እውቅና እና ምስጋና የበለጠ ሞራል ሆኖ የተሻለ ለመፈጸም እንደሚያነሳሳ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ሰራተኞቹ እስከዛሬ ያሳዩትን ትጋት የበለጠ በማጠናከር ለከተማዋ የመንገድ ሽፋን እድገት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በበጀት አመቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ብዙ ቅሬታ የነበረባቸውን ፕሮጀክቶች በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃቱን ያስታወሱት ደግሞ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሙህዲን ረሻድ ናቸው።
አሁን ለተገኘው ውጤትም በትጋት የሰሩት የባለስልጣኑ ሰራተኞችና አመራሮች ምስጋና እንደሚገባቸው ገልጸዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ2017 በጀት አመት ከፍተኛ የህዝብ የመልካም አስተዳደር ቅሬታ ሲነሳባቸው የነበሩትን ጨምሮ 31 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ርዝመት ያላቸው 13 የመንገድ ፕሮጀክቶች እና 8 ድልድዮች ተጠናቀው ለምረቃ እንዲበቁ ማድረጉ ተገልጿል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026