
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማን የመንገድ መሰረተ ልማት በሚፈለገው ደረጃ ለማሳደግ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ሰራተኞችና በየደረጃው የሚገኘው አመራር የበለጠ መትጋት እንዳለባቸው ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ2017 በጀት አመት በመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታው መስክ ለተገኘው ስኬት ለሰራተኞቹ የምስጋናና የእውቅና መርሃ-ግብር አካሂዷል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ከንቲባዋ እንደገለጹት የከተማዋ የመንገድ ሽፋን ገና ብዙ መስራትን የሚጠይቅ ነው።

በዚህ ሒደት የባለስልጣኑ ሰራተኞች አሁን ለተደረሰበት ደረጃ ያሳዩት ትጋትና የስራ ተነሳሽነት የሚያስመሰግናቸው እንደሆነ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
ከተማችን አለም አቀፍ ተወዳዳሪ እስከምትሆን ድረስ 24/7 ነው የምንሰራው ያሉት ከንቲባዋ ለሰራተኞቹ የተሰጠው እውቅና እና ምስጋና የበለጠ ሞራል ሆኖ የተሻለ ለመፈጸም እንደሚያነሳሳ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ሰራተኞቹ እስከዛሬ ያሳዩትን ትጋት የበለጠ በማጠናከር ለከተማዋ የመንገድ ሽፋን እድገት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በበጀት አመቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ብዙ ቅሬታ የነበረባቸውን ፕሮጀክቶች በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃቱን ያስታወሱት ደግሞ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሙህዲን ረሻድ ናቸው።
አሁን ለተገኘው ውጤትም በትጋት የሰሩት የባለስልጣኑ ሰራተኞችና አመራሮች ምስጋና እንደሚገባቸው ገልጸዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ2017 በጀት አመት ከፍተኛ የህዝብ የመልካም አስተዳደር ቅሬታ ሲነሳባቸው የነበሩትን ጨምሮ 31 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ርዝመት ያላቸው 13 የመንገድ ፕሮጀክቶች እና 8 ድልድዮች ተጠናቀው ለምረቃ እንዲበቁ ማድረጉ ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026