የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ

Jul 10, 2025

IDOPRESS

ሰመራ ፤ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)፡- በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ አወል አብዱ የበጀት ዓመቱን የገቢ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸው፤ በዚህም ከዕቅድ በላይ 6 ቢሊዮን 40 ሚሊዮን 398 ሺህ 943 ብር መሠብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር 46 በመቶ ልዩነት ያለውና 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።

ገቢው የተሰበሰበው ከቀጥታ ታክስ፣ ቀጥታ ካልሆነ ታክሰና ታክሰ ካልሆኑ የገቢ አርዕሰት መሆኑንም ኃላፊው ተናግረዋል።

ለበጀት ዓመቱ ከዕቅድ በላይ ክንውን ተከታታይነት ያለውና በየደረጃው ያሉ የአመራርና የዘርፉ ባለሙያዎች ቁርጠኝነት የታከለበት ስራ በመከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።

በበጀት ዓመቱ ደረሰኝ ካለመቁረጥ ጀምሮ በህገ ወጥነት የተሳተፉ ከ1 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ የእርምት እርምጃ መወሰዱንም አቶ አወል አስታውቀዋል።

አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የስነ-ምግባር ጥሰቶችን በማረም ህገ ወጥነትን ወደ ህግ የመመለስ ስራዎች መከናወኑንም አክለዋል።

ክልሉ ካለው እምቅ አቅም ጋር የተመጣጠነ ገቢ ለመሰብሰብ በቀጣዩ ዓመት ትኩረት የተሰጠ መሆኑንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026