
ሰመራ ፤ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)፡- በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ አወል አብዱ የበጀት ዓመቱን የገቢ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸው፤ በዚህም ከዕቅድ በላይ 6 ቢሊዮን 40 ሚሊዮን 398 ሺህ 943 ብር መሠብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር 46 በመቶ ልዩነት ያለውና 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
ገቢው የተሰበሰበው ከቀጥታ ታክስ፣ ቀጥታ ካልሆነ ታክሰና ታክሰ ካልሆኑ የገቢ አርዕሰት መሆኑንም ኃላፊው ተናግረዋል።
ለበጀት ዓመቱ ከዕቅድ በላይ ክንውን ተከታታይነት ያለውና በየደረጃው ያሉ የአመራርና የዘርፉ ባለሙያዎች ቁርጠኝነት የታከለበት ስራ በመከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።
በበጀት ዓመቱ ደረሰኝ ካለመቁረጥ ጀምሮ በህገ ወጥነት የተሳተፉ ከ1 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ የእርምት እርምጃ መወሰዱንም አቶ አወል አስታውቀዋል።
አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የስነ-ምግባር ጥሰቶችን በማረም ህገ ወጥነትን ወደ ህግ የመመለስ ስራዎች መከናወኑንም አክለዋል።
ክልሉ ካለው እምቅ አቅም ጋር የተመጣጠነ ገቢ ለመሰብሰብ በቀጣዩ ዓመት ትኩረት የተሰጠ መሆኑንም አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026