
ገንዳ ውሃ ፤ሃምሌ 3/2017 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ጎንደር ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከእጣንና ሙጫ ሽያጭ ከ108 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የምዕራብ ጎንደር ዞን የአካባቢና ደን ጥበቃ ተጠሪ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በጽህፈት ቤቱ የአካባቢ የህግ ተከባሪነትና የማህበረሰብ ተፅዕኖ ግምገማ ቡድን መሪ አቶ ሀብታሙ አድጎ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ ከፍተኛ የሆነ የእጣንና የሙጫ ደን ሀብት አለ።
በዞኑ ከሚገኘው 760 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ በደን የተሸፈነ መሬት ከ234 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው በእጣንና ሙጫ ዛፍ የተሸፈነ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ17 ማህበራትና ባለሃብቶች 5 ሺህ 80 ኩንታል ምርት በመሰብሰብና ለገበያ በማቅረብ ከ108 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል።
አምራቾች ካገኙት ገቢ በተጨማሪ በሮያሊቲ ታክስ ክፍያ ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስገኘታቸውን አስረድተዋል።
በዘርፉ ለ722 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል የተፈጠረላቸው መሆኑን ጠቁመው ይህም ዘርፉ ከገቢ ባሻገር ዋና የስራ እድል መፍጠሪያ ሆኖ እያገለገለ መሆኑን ገልፀዋል።
በዞኑ በመተማ፣ በቋራና በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳዎች የተመረተው የእጣንና ሙጫ ምርት በላኪዎች በኩል ወደ ውጭ ተልኮ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ መሆኑን ጠቁመዋል።
በመተማ ወረዳ ሌንጫ ቀበሌ አዲስ ህይወት የህብረት ስራ ማህበር ሰብሳቢ የሆኑት አቶ በየነ ውቤ እንዳሉት ማህበሩ 60 አባላቱን በማሳተፍ በበጀት ዓመቱ 229 ኩንታል እጣንና ሙጫ ማምረት ችሏል።
ያመረቱትን እጣንና ሙጫ አንዱን ኩንታል በ53 ሺህ ብር በጨረታ በመሸጥ ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የእጣን ዛፉ ዘላቂ ጥቅም እንዲሰጥም ባገኙት ስልጠናና ግንዛቤ ፈጠራ በመመስረት በማምረት ሂደትና ከምርት በኋላ ተገቢውን እንክብካቤ እያደረጉ መሆኑንም አስረድተዋል።
በዚሁ ወረዳ የላይኛው ለምለም ተራራ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ማህበር አባል አቶ ሙሀመድ አደም በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ 109 ኩንታል ምርት በመሰብሰብ ለገበያ አቅርበው በመሸጥ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ማህበራቸው 190 አባላት ያለው ሲሆን በቀጣይ የተሻለ ምርት ለማምረት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
የእጣንና ሙጫ ደንን ለማስፋፋት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑም ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026