
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ "ዙሪያ" የተሰኘው መተግበሪያ የንግድ ስርዓቱን በማቀላጠፍ፣ የተገልጋዮችን ጊዜና ገንዘብ በመቆጠብ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና ገለጹ።
ኢትዮ ቴሌኮም፣ ዳሽን ባንክ እና ኢታ ሶሊዩሽን የንግድ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን የሚያቀላጥፍ "ዙሪያ" የተሰኘ የቢዝነስ አውቶሜሽን ሶሉሽን መተግበሪያ ይፋ አድርገዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ችፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና እንዳሉት፣ መተግበሪያው የንግድ ስርዓቱን በማዘመን የተገልጋዮችን ጊዜና ገንዘብ የሚቆጥብ ነው።
የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በቀላሉ ለማወቅ እንደሚረዳና ለነጋዴዎች የተሻለ የክፍያ መፈጸሚያ አማራጭ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
"ዙሪያ" ለአጠቃቃቀም ቀላል እና ፈጣን፣ ደህነንቱ የተረጋገጠ መሆኑንም ጨምረው አንስተዋል።
የውጪ እና የሀገር ውስጥ የክፍያ ካርዶችን እንደሚቀበልና የሂሳብ ስራን ቀላል እንደሚያደርግም አስታውቀዋል።
በወረቀትና በማሽን ይሰራ የነበረውን የክፍያ ስርዓት ወደ አንድ ወጥ አተገባበር የሚያመጣ መተግበሪያ እንደሆነም ጠቁመዋል።
መተግበሪያው የንግድ ስርዓቱንና አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026