
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 8/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) ገለጹ።
አገልግሎቱ ዛሬ የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ-ዝግጅት ተግባራት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሒዷል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ድርጀቶች ቆጠራ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።
በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) በ2018 ዓ.ም የሚጀመረውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ በመግለጫቸው፤ አገልግሎቱ ከ2016 ዓ.ም እስከ 2018 ዓ.ም የስታስቲክስ ልማት ፕሮግራም ቀርጾ ሲንቀሳቀስ ቆይቷል፡፡
ከልማት መርሃ ግብሮቹ መካከል የኢትዮጵያ የስነ ህዝብና ጤና ጥናት፤ የኢትዮጵያ የግብርና ቆጠራ፣ ብሔራዊ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናትና የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ዋና ዋናዎቹ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከነዚህ መካከል የኢትዮጵያ የስነ ህዝብና ጤና ጥናት ማለቁን ጠቁመው፤ የኢትዮጵያ የግብርና ቆጠራ እና ብሔራዊ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናት በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በመስከረም እንደሚጀመር ገልጸው፤ በቆጠራው በመላው አገሪቷ የሚገኙ ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ ኢንተርፕራይዞች እንደሚካተቱ ተናግረዋል።
ከቆጠራው የሚገኙ መረጃዎች በዘርፉ ለሚዘጋጁ እቅዶች፣ ፖሊሲዎች እና ስትራቴጂ ትክክለኛ ግብዓት ሆነው እንደሚያገለግሉ ጠቁመዋል፡፡
ስለሆነም በመላው አገሪቷ የሚገኙ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ቆጠራው የሚጀመራው በአዲስ ዓመት መግቢያ መሆኑን ተገንዝበው ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ አስተባባሪ ኮሚቴ የቅድመ ዝግጅት ስራውን ዛሬ በይፋ መጀመሩን ገልጸው፤ ስራው የስነ ጥናት ዘዴውንና ሽፋኑን እንደሚወስንም ነው የተናገሩት።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026