
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017 (ኢዜአ):-በከተማ አስተዳደሩ የሚዘጋጁ ኤግዚቢሽን እና ባዛር የአምራች እና የሸማቹን የገበያ ትስስር እያጠናከሩ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ ገለጹ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ያዘጋጀውና ከሃምሌ 7 እስከ ሃምሌ 11/2017 ዓ/ም በኤግዚቢሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው 2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛር በዛሬው እለት ተጠናቋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቢሮው የነዋሪውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ከዚህ ውስጥ የንግድ ስርአቱን ቀልጣፋ እንዲሆን አምራች እና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት በኩል ውጤታማ ስራ መሰራቱን ለአብነት አንስተዋል፡፡
2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛርም የነዋሪውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
ለ5 ቀናት በቆየው ኤግዚቢሽን እና ባዛር የአገር ውስጥ ምርቶችና አገልግሎቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ለህብረተሰቡ ትልቅ ፋይዳ ማስገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡
በኤግዚቢሽን እና ባዛሩ በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት መፈጸማቸውን አንስተው ከ43 ሚሊየን ብር በላይ ግብይት መከናወኑንም አስታውቀዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ፍስሃ ጥበቡ በበኩላቸው፤ ባዛሩ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ ትስስር የተፈጠረበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡

ቢሮው አቅራቢዎችና ሸማቾች በቀጥታ የሚገበያዩበት ምቹ ሁኔታን የመፍጠር ተግባራትን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡
ከሸማቾች መካከል አልማዝ አበበ እንደገለጸችው ከባዛሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን በመግዛት ተጠቃሚ መሆኗን ተናግራለች፡፡

ምርታቸውን በባዛሩ ያቀረቡት አቶ ደረጀ ጋሪ በበኩላቸው፤ ባዛሩ መዘጋጀቱ ምርቶቻቸውን በቀጥታ ለህብረተሰቡ እንዲያቀርቡ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026