
አሶሳ፤ ሐምሌ 13/2017(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተያዘው የመኸር ወቅት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
በክልሉ በመኸር እርሻ ከሚለማው መሬት ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱም ተመላክቷል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ አቡራሞ ወረዳ አንጉላሎ ቀበሌ ከ3 ሺህ 200 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ በኩታ-ገጠም እየለማ ያለ የበቆሎ ማሳን ዛሬ ተመልክተዋል።

አቶ አሻድሊ በዚህ ወቅት እንደገለጹት አርሶ አደሩ ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ የግብርና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
የአርሶ አደሩ በኩታ ገጠም የማልማት ልምዱ እያደገ መሆኑን ጠቁመው፣ በተያዘው የመኸር ወቅት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
እስካሁንም ከ1 ሚሊዮን 500 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን አቶ አሻድሊ ጠቁመው፣ ከመኸር እርሻ ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል።

የዘንድሮው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ በክልሉ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በርብርብ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወረዳው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴን ከመመልከት ጎን ለጎን ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026