
አሶሳ፤ ሐምሌ 13/2017(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተያዘው የመኸር ወቅት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
በክልሉ በመኸር እርሻ ከሚለማው መሬት ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱም ተመላክቷል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ አቡራሞ ወረዳ አንጉላሎ ቀበሌ ከ3 ሺህ 200 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ በኩታ-ገጠም እየለማ ያለ የበቆሎ ማሳን ዛሬ ተመልክተዋል።

አቶ አሻድሊ በዚህ ወቅት እንደገለጹት አርሶ አደሩ ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ የግብርና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
የአርሶ አደሩ በኩታ ገጠም የማልማት ልምዱ እያደገ መሆኑን ጠቁመው፣ በተያዘው የመኸር ወቅት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
እስካሁንም ከ1 ሚሊዮን 500 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን አቶ አሻድሊ ጠቁመው፣ ከመኸር እርሻ ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል።

የዘንድሮው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ በክልሉ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በርብርብ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወረዳው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴን ከመመልከት ጎን ለጎን ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026