
አዲስ አበባ፤ሐምሌ14/2017(ኢዜአ)፡-የሆርቲካልቸር ስትራቴጂ እና የእንሰት ልማት ፍላግሺፕ ፕሮግራም በዘርፉ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም ለኢኮኖሚ እድገትና ለምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትና ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ።
ብሔራዊ የሆርቲካልቸር ስትራቴጂ እና የእንሰት ፍላግሺፕ ፕሮግራም ማብሰሪያ መድረክ እየተካሄደ ነው።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ግብርናው ለጠቅላላ ዓመታዊ ምርት፣ለአግሮ ኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት እና ለውጭ ምንዛሬ ግኝት ካለው ከፍተኛ አስተዋፅኦ በተጨማሪ በርካታ የሥራ ዕድል ለመፍጠር አስችሏል፡፡
በመሆኑም የግብርና ልማቱን በተሻሻለ ቴክኖሎጂ እና ዕውቀት መደገፍ አስፈላጊ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
በግብርናው ዘርፍ የሪፎርም ስራዎችን በማከናወንና የዘርፉን ፀጋዎች በመጠቀም በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው ብለዋል።
በዚህም የተመዘገቡ ውጤቶችን በማስቀጠል ሀገራዊ አጀንዳዎችን ለማሳካት ቀጣይነት ባለው መልኩ የሚሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የሆርቲካልቸር ንኡስ ዘርፍ ካለው ኢኮኖሚያዊና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች አኳያ ቀጣይ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመላክተዋል።
የሆርቲካልቸር ንዑስ ዘርፍ የምግብና የሥርዓት-ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ለአብነት በ2016/17 ዓ.ም ወደ ውጭ ከተላከ 286 ሺህ ቶን የሆርቲካልቸር ምርት 565 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መገኘቱን አስታውቀዋል።
በመሆኑም የሆርቲካልቸር ንኡስ ዘርፍ የምርምርና ኤክስቴንሽን ስራን በማጠናከር እና የድህረምርት አያያዝና የገበያ መሰረተ ልማቶችን በማሻሻል ለሀገራዊ ኢኮኖሚያለውን አስተዋፅኦ ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ለዚህ የሚረዳ ሀገራዊ የሆርቲካልቸር ስትራቴጂ እና የእንሰት ልማት ፍላግሺፕ ፕሮግራም ሰነድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ስትራቴጂው በሆርቲካልቸር ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም በሚፈለገው ደረጃ በመጠቀም ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ለምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትና መረጋገጥ የጎላ ሚና እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026