
አዲስ አበባ፤ሐምሌ14/2017(ኢዜአ)፡-የሆርቲካልቸር ስትራቴጂ እና የእንሰት ልማት ፍላግሺፕ ፕሮግራም በዘርፉ ያለውን እምቅ አቅም በመጠቀም ለኢኮኖሚ እድገትና ለምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትና ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ።
ብሔራዊ የሆርቲካልቸር ስትራቴጂ እና የእንሰት ፍላግሺፕ ፕሮግራም ማብሰሪያ መድረክ እየተካሄደ ነው።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ግብርናው ለጠቅላላ ዓመታዊ ምርት፣ለአግሮ ኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት እና ለውጭ ምንዛሬ ግኝት ካለው ከፍተኛ አስተዋፅኦ በተጨማሪ በርካታ የሥራ ዕድል ለመፍጠር አስችሏል፡፡
በመሆኑም የግብርና ልማቱን በተሻሻለ ቴክኖሎጂ እና ዕውቀት መደገፍ አስፈላጊ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
በግብርናው ዘርፍ የሪፎርም ስራዎችን በማከናወንና የዘርፉን ፀጋዎች በመጠቀም በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው ብለዋል።
በዚህም የተመዘገቡ ውጤቶችን በማስቀጠል ሀገራዊ አጀንዳዎችን ለማሳካት ቀጣይነት ባለው መልኩ የሚሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የሆርቲካልቸር ንኡስ ዘርፍ ካለው ኢኮኖሚያዊና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች አኳያ ቀጣይ የትኩረት ማዕከል መሆኑን አመላክተዋል።
የሆርቲካልቸር ንዑስ ዘርፍ የምግብና የሥርዓት-ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ለአብነት በ2016/17 ዓ.ም ወደ ውጭ ከተላከ 286 ሺህ ቶን የሆርቲካልቸር ምርት 565 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መገኘቱን አስታውቀዋል።
በመሆኑም የሆርቲካልቸር ንኡስ ዘርፍ የምርምርና ኤክስቴንሽን ስራን በማጠናከር እና የድህረምርት አያያዝና የገበያ መሰረተ ልማቶችን በማሻሻል ለሀገራዊ ኢኮኖሚያለውን አስተዋፅኦ ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ለዚህ የሚረዳ ሀገራዊ የሆርቲካልቸር ስትራቴጂ እና የእንሰት ልማት ፍላግሺፕ ፕሮግራም ሰነድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ስትራቴጂው በሆርቲካልቸር ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም በሚፈለገው ደረጃ በመጠቀም ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ለምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትና መረጋገጥ የጎላ ሚና እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026