የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በደብረ ብርሃን ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 25 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል

Jul 22, 2025

IDOPRESS

ደብረ ብርሃን፤ ሐምሌ 14/2017(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 25 ኢንዱስትሪዎች ወደማምረት መሸጋገራቸውን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው የ2017 ዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጸምን የሚገመግምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ላይ ያተኮረ መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።

የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ብርሃን ገብረህይወት እንደገለጹት በከተማው የሚከናወኑ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ሥራዎች ለሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ሚና አላቸው።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዘርፉን ለማጠናከር በተደረገ ጥረት በከተማው 25 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 232 ባለሃብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ጠቁመው፣ ባለሀብቶቹ ወደሥራ ሲገቡ ከ21 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል ይፈጥራሉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን መሰረት በማድረግ በተካሄደ ጥረትም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከውጭ የሚገባን ተኪ ምርትና ለወጭ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከልም አቶ አየለ ደስታ እንደገለጹት በአካባቢው በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፍ የታየው መነቃቃት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ ወይዘሮ ጽጌ ዋሪ በበኩላቸው በአካባቢው ያለውን ጸጋ ለማስተዋወቅ የተሰራው ሥራ የባለሀብቶች ፍሰት እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል።


በደብረ ብርሃን ከተማ በበጀት ዓመቱ በኢንቨስትመንት ዘርፍ በአጠቃላይ ለ5 ሺህ 113 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ከመምሪያው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026