
ደብረ ብርሃን፤ ሐምሌ 14/2017(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 25 ኢንዱስትሪዎች ወደማምረት መሸጋገራቸውን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው የ2017 ዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጸምን የሚገመግምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ላይ ያተኮረ መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።
የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ብርሃን ገብረህይወት እንደገለጹት በከተማው የሚከናወኑ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ሥራዎች ለሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ሚና አላቸው።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዘርፉን ለማጠናከር በተደረገ ጥረት በከተማው 25 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 232 ባለሃብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ጠቁመው፣ ባለሀብቶቹ ወደሥራ ሲገቡ ከ21 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል ይፈጥራሉ ብለዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን መሰረት በማድረግ በተካሄደ ጥረትም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከውጭ የሚገባን ተኪ ምርትና ለወጭ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።
ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከልም አቶ አየለ ደስታ እንደገለጹት በአካባቢው በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፍ የታየው መነቃቃት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው ብለዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ ወይዘሮ ጽጌ ዋሪ በበኩላቸው በአካባቢው ያለውን ጸጋ ለማስተዋወቅ የተሰራው ሥራ የባለሀብቶች ፍሰት እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል።

በደብረ ብርሃን ከተማ በበጀት ዓመቱ በኢንቨስትመንት ዘርፍ በአጠቃላይ ለ5 ሺህ 113 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ከመምሪያው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026