የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በደብረ ብርሃን ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 25 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል

Jul 22, 2025

IDOPRESS

ደብረ ብርሃን፤ ሐምሌ 14/2017(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 25 ኢንዱስትሪዎች ወደማምረት መሸጋገራቸውን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው የ2017 ዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጸምን የሚገመግምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ላይ ያተኮረ መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።

የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ብርሃን ገብረህይወት እንደገለጹት በከተማው የሚከናወኑ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ሥራዎች ለሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ሚና አላቸው።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዘርፉን ለማጠናከር በተደረገ ጥረት በከተማው 25 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 232 ባለሃብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ጠቁመው፣ ባለሀብቶቹ ወደሥራ ሲገቡ ከ21 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል ይፈጥራሉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን መሰረት በማድረግ በተካሄደ ጥረትም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከውጭ የሚገባን ተኪ ምርትና ለወጭ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከልም አቶ አየለ ደስታ እንደገለጹት በአካባቢው በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፍ የታየው መነቃቃት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ ወይዘሮ ጽጌ ዋሪ በበኩላቸው በአካባቢው ያለውን ጸጋ ለማስተዋወቅ የተሰራው ሥራ የባለሀብቶች ፍሰት እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል።


በደብረ ብርሃን ከተማ በበጀት ዓመቱ በኢንቨስትመንት ዘርፍ በአጠቃላይ ለ5 ሺህ 113 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ከመምሪያው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026