የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የክልሉ የግብርና ልማት ሥራዎች በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን እንቅስቃሴ የሚያፋጥኑ ናቸው

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፣ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ልማት ሥራዎች በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን እንቅስቃሴ እንደሚያፋጥኑ ተገለጸ።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ለኢዜአ እንደገለጹት በምግብ ራስን መቻል የሕልውና ጉዳይ ነው።


የኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነት ሊረጋገጥ የሚችለው ከተረጂነት መላቀቅ ሲቻል ብቻ መሆኑን ያነሱት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፣ መንግስት ይህን ለማሳካት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት እየተሠራ ያለው ሥራ ውጤት እያሳየ መሆኑንም ተናግረዋል።

በክልሉም ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠል ዘንድሮ ከ5 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ስንዴ እና ከ36 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ሩዝ መልማቱን ጠቅሰዋል።

ቀደም ሲል በክልሉ ሩዝና ስንዴ ማልማት እንዳልተለመደ አስታውሰው፣ ለክልሉ አርሶ አደሮች አዳዲስ ሰብሎችን በማስተዋወቅ በምግብ ራስን ለመቻል ጠንካራ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

ክልሉ ለግብርና ሥራዎች ያለውን ምቹ የአየር ጸባይ ተጠቅሞ በሁሉም የሰብል አይነቶች ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አቶ ማስረሻ አንስተዋል።

ዘንድሮ እንደ ክልል ከ750 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ20 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ምርት የማምረት ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጸው ይህም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል።

በክልሉ ቤንች ሸኮ ዞን የጉራፈርዳ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ተስፋ አማን ሩዝን በኩታገጠም በማልማት ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረው፣ ለዚህም መንግስት የሰጠው የልማት አቅጣጫ ትልቁን ድርሻ ይይዛል ብለዋል።

በዘንድሮ በበልግ እርሻ በሁለት ሄክታር ማሳ ላይ ካለሙት የሩዝ ማሳ ከ70 ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ተገቢ እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ሩዝ፣ በቆሎና ሌሎች ሰብሎችን በማልማት ለምግብ ፍጆታ ከማዋል ባሻገር ለገበያ በማቅራብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን የተናገሩት ሌላው የወረዳው አርሶ አደር ጉችዬ ተመስገን ናቸው።

ዘንድሮ የተሟላ ግብዓት ተጠቅመው ካለሙት የእርሻ ማሳ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

በክልሉ በተለያዩ አማራጮች እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ሥራዎች የበርካታ ዜጎችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ከማሳደግ ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል እሳቤን ለማረጋገጥ እያገዙ መሆናቸው ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026