የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የክልሉ የግብርና ልማት ሥራዎች በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን እንቅስቃሴ የሚያፋጥኑ ናቸው

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፣ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ልማት ሥራዎች በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን እንቅስቃሴ እንደሚያፋጥኑ ተገለጸ።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ለኢዜአ እንደገለጹት በምግብ ራስን መቻል የሕልውና ጉዳይ ነው።


የኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነት ሊረጋገጥ የሚችለው ከተረጂነት መላቀቅ ሲቻል ብቻ መሆኑን ያነሱት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፣ መንግስት ይህን ለማሳካት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት እየተሠራ ያለው ሥራ ውጤት እያሳየ መሆኑንም ተናግረዋል።

በክልሉም ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠል ዘንድሮ ከ5 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ስንዴ እና ከ36 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ሩዝ መልማቱን ጠቅሰዋል።

ቀደም ሲል በክልሉ ሩዝና ስንዴ ማልማት እንዳልተለመደ አስታውሰው፣ ለክልሉ አርሶ አደሮች አዳዲስ ሰብሎችን በማስተዋወቅ በምግብ ራስን ለመቻል ጠንካራ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

ክልሉ ለግብርና ሥራዎች ያለውን ምቹ የአየር ጸባይ ተጠቅሞ በሁሉም የሰብል አይነቶች ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አቶ ማስረሻ አንስተዋል።

ዘንድሮ እንደ ክልል ከ750 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ20 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ምርት የማምረት ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጸው ይህም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል።

በክልሉ ቤንች ሸኮ ዞን የጉራፈርዳ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ተስፋ አማን ሩዝን በኩታገጠም በማልማት ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረው፣ ለዚህም መንግስት የሰጠው የልማት አቅጣጫ ትልቁን ድርሻ ይይዛል ብለዋል።

በዘንድሮ በበልግ እርሻ በሁለት ሄክታር ማሳ ላይ ካለሙት የሩዝ ማሳ ከ70 ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ተገቢ እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ሩዝ፣ በቆሎና ሌሎች ሰብሎችን በማልማት ለምግብ ፍጆታ ከማዋል ባሻገር ለገበያ በማቅራብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን የተናገሩት ሌላው የወረዳው አርሶ አደር ጉችዬ ተመስገን ናቸው።

ዘንድሮ የተሟላ ግብዓት ተጠቅመው ካለሙት የእርሻ ማሳ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

በክልሉ በተለያዩ አማራጮች እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ሥራዎች የበርካታ ዜጎችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ከማሳደግ ባለፈ በምግብ ራስን የመቻል እሳቤን ለማረጋገጥ እያገዙ መሆናቸው ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026