የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 162 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

Jul 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 162 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።

ገቢው የተገኘው ከድምጽ ጥሪ፣ ከኢንተርኔት አገልግሎት፣ ከቫስ፣ ከመሠረተ ልማት ማጋራት፣ ከቴሌኮም ቁሳቁስ ሽያጭና ከሌሎች ምንጮች መሆኑንም ገልጿል።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ፥ የኩባንያውን የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምና መሪ የሶስት ዓመት የእድገት ስትራቴጂ ማጠቃለያ ሪፖርት ለመገናኛ ብዙኃን ይፋ አድርገዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም ከሶስት ዓመት በፊት የቴሌኮም እና የዲጂታል አገልግሎትን ማሳደግ የሚያስችል መሪ የሶስት ዓመት የእድገት ስትራቴጂ አዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰዋል።

ኩባንያው ከቴሌኮም አገልግሎት ባሻገር በዲጂታላይዜሽን በኩል አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን አመላክተዋል።

የቴሌኮም አገልግሎት አሰጣጡን ከማስፋትና ጥራቱን ከማሳደግ አኳያ ከፍተኛ እድገት መመዝገቡንም ነው ዋና ስራ አስፈጻሚዋ የገለጹት።

ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረትም ትርጉም ያለው ስራ መሠራቱን አንስተዋል።

በመሪ የሶስት ዓመት የእድገት ስትራቴጂ ደግሞ 26 ከተሞችን በ5ጂ ኔት ወርክ እንዲሁም 936 ከተሞችን በ4ጂ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

በዚህም በመላ ሀገሪቱ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን የፈጣን ኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ምህዳር መፈጠሩን ተናግረዋል።

በ2017 በጀት ዓመት 1ሺህ 683 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎች መገንባታቸውንም ነው የጠቀሱት።

በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ10ሺህ በላይ የሞባይል ጣቢያዎች ተተክለው አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙም አመላክተዋል።

በበጀት ዓመቱ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፥ 162 ቢሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026