
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዳስትሪ ፓርኮች 16 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው ተኪ ምርት ማምረት መቻሉን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ገለፀ።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ከነበረበት 47 በመቶ ወደ 65 በመቶ ማሳደግ ችሏል፡፡
በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ዘርፍ ስራ አስፈፃሚ ዘመን ጁነዲ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገሪቱ ያሉት ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች 16 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው ተኪ ምርት ማምረት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡
የመከላከያ ሠራዊትና የሌሎች የፀጥታ አካላትን የደንብ ልብሶች ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ማምረት መቻሉን ጠቁመው፤ ይህም ኢንዱስትሪዎቹ በሀገር ውስጥ ከፍተኛ የገበያ ዕድል እንዲያገኙ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ45ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል፡፡
በልዩ የኢንዱስትሪ ዞኖቹ በፋርማሲቲካል፣ በኮንስትራክሽን እና የኬሚካል ኢንዱስትሪ ዘርፎችን ተኪ ምርቶችን በስፋት ለማምረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር የውጪ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ መቻሉንም ተናግረዋል፡፡
በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ጨርቃጨርቅን ጨምሮ፣ የግብርና ምርት ማቀነባበር፣ የፋርማሲቲካል፣ የኬሚካል እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎችም እየተስፋፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡
በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የኢትዮጵያውያን ባለሃብቶች ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመው፤ አሁን ላይ ከ50 በመቶ በላይ መድረሱንም ገልጸዋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ሀገራት ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችን በተመለከተ የግንዛቤ ስራዎች በመሰራታቸው ተጨባጭ ለውጦች ማምጣት መቻላቸውን ጠቁመዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ በመላው ኢትዮጵያ ከሚያስተዳድራቸው 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮች መካከል 11 የሚሆኑት ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን መሸጋገራቸው ይታወቃል፡፡
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026