የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች 16 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው ተኪ ምርት ተመርቷል

Jul 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዳስትሪ ፓርኮች 16 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው ተኪ ምርት ማምረት መቻሉን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ገለፀ።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ከነበረበት 47 በመቶ ወደ 65 በመቶ ማሳደግ ችሏል፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ዘርፍ ስራ አስፈፃሚ ዘመን ጁነዲ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሀገሪቱ ያሉት ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች 16 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው ተኪ ምርት ማምረት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡

የመከላከያ ሠራዊትና የሌሎች የፀጥታ አካላትን የደንብ ልብሶች ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ማምረት መቻሉን ጠቁመው፤ ይህም ኢንዱስትሪዎቹ በሀገር ውስጥ ከፍተኛ የገበያ ዕድል እንዲያገኙ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ45ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል፡፡

በልዩ የኢንዱስትሪ ዞኖቹ በፋርማሲቲካል፣ በኮንስትራክሽን እና የኬሚካል ኢንዱስትሪ ዘርፎችን ተኪ ምርቶችን በስፋት ለማምረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር የውጪ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ መቻሉንም ተናግረዋል፡፡

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ጨርቃጨርቅን ጨምሮ፣ የግብርና ምርት ማቀነባበር፣ የፋርማሲቲካል፣ የኬሚካል እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎችም እየተስፋፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የኢትዮጵያውያን ባለሃብቶች ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመው፤ አሁን ላይ ከ50 በመቶ በላይ መድረሱንም ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ የዓለም ሀገራት ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችን በተመለከተ የግንዛቤ ስራዎች በመሰራታቸው ተጨባጭ ለውጦች ማምጣት መቻላቸውን ጠቁመዋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ በመላው ኢትዮጵያ ከሚያስተዳድራቸው 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮች መካከል 11 የሚሆኑት ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን መሸጋገራቸው ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026