የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የቴክኖሎጂ እውቀት እና ክህሎት ለማዳበር ረድቶናል - የመንግስት ሰራተኞች

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አምቦ፤ ሐምሌ 18/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮ ኮደርስ ዲጂታል ስልጠና በፊት ያለንን የቴክኖሎጂ እውቀት እና ክህሎት ለማዳበር ረድቶናል ሲሉ በምዕራብ ሸዋ ዞን ሰልጣኝ መንግስት ሰራተኞች ገለፁ።

የኢትዮ ኮደርስ ዲጂታል ስልጠና የተከታተሉና ኢዜአ ያነጋገራቸው የመንግስት ሰራተኞች እንዳሉት ስልጠናው ዘመናዊ የዲጂታል መሣሪያዎችን በተግባር ለማዋል በማስቻሉ ክህሎታቸውን በማሳደግ ውጤታማ የሚያደርግ ነው።

ከሰልጣኖች መካከል አቶ ደረጀ ፍቃዱ ፤ ስልጠናውን በመውሰዳቸው በጣም መደሰታቸውን ተናግረው፣ ሰራተኞችና ወጣቶች ችሎታቸውን ለማሳደግና አዳዲስ የስራ እድሎችን ለመፍጠር ስልጠናውን መከታተል እንደሚገባ አንስተዋል።

ሌላው ሰልጣኝ አቶ ራፌራ ደበሳ በበኩላቸው፤ በዚህ በቴክኖሎጂ ዘመን ስልጠናውን መውሰዳቸው እንዳስደሰታቸው ጠቅሰው በዚህም የነበራቸውን ክህሎትና ዕውቀት እንዳዳበረላቸው ተናግረዋል።


የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወሰደችው ወጣት ገላኔ መልካ በበኩሏ፤ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በዲጂታል ዘመኑ ራሷን ብቁ በማድረግ ተወዳዳሪ ለመሆንና የቴክኖሎጂ ክህሎቷን ለማዳበር እንዳስቻላት ተናግራለች።


የምዕራብ ሸዋ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ አዲሷ ሻንቆ፤ በዞኑ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለመንግስት ሰራተኞችና ወጣቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን ለማዳበር ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።

ስልጠናው የቴክኖሎጂ ትስስር በመፍጠርና የወጣቶችን አቅም በማሳደግ እንዲሁም አዳዲስ ስራ ለመፍጠር አይነተኛ ሚና ያለው መሆኑን ጠቅሰው በዞኑ ፍላጎት ያላቸውን የህብረተሰብ አካላት ለማሰልጠን ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።


ስልጠናው በቴክኖሎጂ የበቃ ዜጋን ለመፍጠር አጋዥ በመሆኑ በተለይም ወጣቶች መንግስት ያመቻቸውን እድል በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡

በምዕራብ ሸዋ ዞን በ2017 በጀት ዓመት 29 ሺህ የመንግስት ሰራተኞችና ወጣቶች ስልጠናውን በበየነመረብ በመሰልጠን የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026