
አምቦ፤ ሐምሌ 18/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮ ኮደርስ ዲጂታል ስልጠና በፊት ያለንን የቴክኖሎጂ እውቀት እና ክህሎት ለማዳበር ረድቶናል ሲሉ በምዕራብ ሸዋ ዞን ሰልጣኝ መንግስት ሰራተኞች ገለፁ።
የኢትዮ ኮደርስ ዲጂታል ስልጠና የተከታተሉና ኢዜአ ያነጋገራቸው የመንግስት ሰራተኞች እንዳሉት ስልጠናው ዘመናዊ የዲጂታል መሣሪያዎችን በተግባር ለማዋል በማስቻሉ ክህሎታቸውን በማሳደግ ውጤታማ የሚያደርግ ነው።
ከሰልጣኖች መካከል አቶ ደረጀ ፍቃዱ ፤ ስልጠናውን በመውሰዳቸው በጣም መደሰታቸውን ተናግረው፣ ሰራተኞችና ወጣቶች ችሎታቸውን ለማሳደግና አዳዲስ የስራ እድሎችን ለመፍጠር ስልጠናውን መከታተል እንደሚገባ አንስተዋል።
ሌላው ሰልጣኝ አቶ ራፌራ ደበሳ በበኩላቸው፤ በዚህ በቴክኖሎጂ ዘመን ስልጠናውን መውሰዳቸው እንዳስደሰታቸው ጠቅሰው በዚህም የነበራቸውን ክህሎትና ዕውቀት እንዳዳበረላቸው ተናግረዋል።

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወሰደችው ወጣት ገላኔ መልካ በበኩሏ፤ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በዲጂታል ዘመኑ ራሷን ብቁ በማድረግ ተወዳዳሪ ለመሆንና የቴክኖሎጂ ክህሎቷን ለማዳበር እንዳስቻላት ተናግራለች።

የምዕራብ ሸዋ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ አዲሷ ሻንቆ፤ በዞኑ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለመንግስት ሰራተኞችና ወጣቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን ለማዳበር ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።
ስልጠናው የቴክኖሎጂ ትስስር በመፍጠርና የወጣቶችን አቅም በማሳደግ እንዲሁም አዳዲስ ስራ ለመፍጠር አይነተኛ ሚና ያለው መሆኑን ጠቅሰው በዞኑ ፍላጎት ያላቸውን የህብረተሰብ አካላት ለማሰልጠን ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

ስልጠናው በቴክኖሎጂ የበቃ ዜጋን ለመፍጠር አጋዥ በመሆኑ በተለይም ወጣቶች መንግስት ያመቻቸውን እድል በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡
በምዕራብ ሸዋ ዞን በ2017 በጀት ዓመት 29 ሺህ የመንግስት ሰራተኞችና ወጣቶች ስልጠናውን በበየነመረብ በመሰልጠን የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ተናግረዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026