
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦በማዕድን ዘርፍ ልማት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ እያስገኙ መሆናቸውን የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ ገለጹ።
የማዕድን ሚኒስቴር ለማዕድን ዘርፍ የሚውሉ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 29 ተሽከርካሪዎችን እና 81 ላፕቶፖችን ለክልሎች ድጋፍ አድርጓል።

ሚኒስቴሩ ድጋፍ ያደረገው ለክልሎች፣ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር፣ ለኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት እና ለማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ነው፡፡
የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ንብረቶቹን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ ድጋፉ የተደረገው በበጀት ዓመቱ ከማዕድን ዘርፍ የተገኘውን ስኬት መሰረት በማድረግ ውጤቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ለማስቻል ነው።
ለክልሎች የተደረገው ድጋፍ የማዕድን ዘርፉ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው አብራርተዋል።
ሚኒስቴሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተለያዩ ማዕድናትን ለውጭ ገበያ በመላክ አበረታች ለውጥ ማስመዝገቡን ገልጸዋል ።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሱ ሞርካ በበኩላቸው፤ የተደረገው ድጋፍ ከዚህ በፊት ያጋጥማቸው የነበረውን የተሸከርካሪ ችግር በማቃለል ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው ነው የገለጹት።
የኦሮሚያ ማዕድን ልማት ባለስልጣን ሃለፊ የጽህፈት ቤት ሃላፊ ታደሰ ተሾመ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ የማዕድን ልማት ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅና ድጋፍ የሚፈልግ ነው።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026