
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦በማዕድን ዘርፍ ልማት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ እያስገኙ መሆናቸውን የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ ገለጹ።
የማዕድን ሚኒስቴር ለማዕድን ዘርፍ የሚውሉ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 29 ተሽከርካሪዎችን እና 81 ላፕቶፖችን ለክልሎች ድጋፍ አድርጓል።

ሚኒስቴሩ ድጋፍ ያደረገው ለክልሎች፣ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር፣ ለኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት እና ለማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ነው፡፡
የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ንብረቶቹን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ ድጋፉ የተደረገው በበጀት ዓመቱ ከማዕድን ዘርፍ የተገኘውን ስኬት መሰረት በማድረግ ውጤቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ለማስቻል ነው።
ለክልሎች የተደረገው ድጋፍ የማዕድን ዘርፉ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው አብራርተዋል።
ሚኒስቴሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተለያዩ ማዕድናትን ለውጭ ገበያ በመላክ አበረታች ለውጥ ማስመዝገቡን ገልጸዋል ።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሱ ሞርካ በበኩላቸው፤ የተደረገው ድጋፍ ከዚህ በፊት ያጋጥማቸው የነበረውን የተሸከርካሪ ችግር በማቃለል ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው ነው የገለጹት።
የኦሮሚያ ማዕድን ልማት ባለስልጣን ሃለፊ የጽህፈት ቤት ሃላፊ ታደሰ ተሾመ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ የማዕድን ልማት ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅና ድጋፍ የሚፈልግ ነው።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026