የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በማዕድን ዘርፍ ልማት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ እያስገኙ ነው

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦በማዕድን ዘርፍ ልማት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ እያስገኙ መሆናቸውን የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ ገለጹ።

የማዕድን ሚኒስቴር ለማዕድን ዘርፍ የሚውሉ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 29 ተሽከርካሪዎችን እና 81 ላፕቶፖችን ለክልሎች ድጋፍ አድርጓል።


ሚኒስቴሩ ድጋፍ ያደረገው ለክልሎች፣ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር፣ ለኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት እና ለማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ነው፡፡

የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ንብረቶቹን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ ድጋፉ የተደረገው በበጀት ዓመቱ ከማዕድን ዘርፍ የተገኘውን ስኬት መሰረት በማድረግ ውጤቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ለማስቻል ነው።

ለክልሎች የተደረገው ድጋፍ የማዕድን ዘርፉ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው አብራርተዋል።

ሚኒስቴሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተለያዩ ማዕድናትን ለውጭ ገበያ በመላክ አበረታች ለውጥ ማስመዝገቡን ገልጸዋል ።

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሱ ሞርካ በበኩላቸው፤ የተደረገው ድጋፍ ከዚህ በፊት ያጋጥማቸው የነበረውን የተሸከርካሪ ችግር በማቃለል ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው ነው የገለጹት።

የኦሮሚያ ማዕድን ልማት ባለስልጣን ሃለፊ የጽህፈት ቤት ሃላፊ ታደሰ ተሾመ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ የማዕድን ልማት ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅና ድጋፍ የሚፈልግ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026