የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የሳይበር ደህንነት ወር “የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ሀሳብ ከጥቅምት 1 ጀምሮ ይከበራል

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፦ ስድስተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር “የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ሀሳብ ከጥቅምት 1 እስከ 30/2018 ዓ.ም እንደሚከበር የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አስታወቀ።

የሳይበር ደህንነት ወር አከባበርን በማስመልከት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግሥት ሃሚድ በሰጡት መግለጫ፥ የሳይበር ጥቃት በዓለም አቀፍ ደረጃ በቁጥርም ሆነ በአይነት በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ ይገኛል ብለዋል።

የሳይበር ደህንነት ወር መከበር ዋነኛ ዓላማው የዜጎችንና የተቋማትን የሳይበር ደህንነት ግንዛቤ የሚያጎለብቱ የንቅናቄ መድረኮችን በማዘጋጀት ሀገራዊ የሳይበር ደህንነት የመከላከል አቅምን ለማሳደግ ነው ብለዋል።

“የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከበረው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህነንት ወር ሁለት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግም ተናግረዋል።

የመጀመሪያው የሃሰተኛ መረጃ ዝግጅት፣ ቁጥጥርና ስርጭትን ለመቆጣጠር እና ለመከላከል ያለመ ንቅናቄ መሆኑን ገልጸዋል።

በሁለተኛ ደረጃ በዲጂታላይዜሽን ደህንነት ጉዞ የተቋማትን የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያስችል ንቅናቄ መሆኑን ተናግረዋል።

6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር አስፈላጊነትም ተቋማት በሰፊዉ ወደ ዲጂታላይዜሽን እየገቡ በመሆኑ ከወዲሁ የሳይበር ደህንነት ዝግጁነታቸዉን መጨመር እንዲችሉ ነው ብለዋል።

የሳይበር ደህንነት ወር የመክፈቻ መርሃ ግብር ጥቅምት 1 ቀን 2018 እንደሚካሄድ በማንሳት ወሩን ሙሉ በተለያዩ ከተሞች የህብረተሰቡን ንቃተ ህሊና የሚያሳድጉ መርሃ ግብሮች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025