🔇Unmute
ወልዲያ፤ መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦ የወልዲያ ከተማና አካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት አባላት ገለጹ።
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር፣ 12ኛ ዓመት፣ 17ኛ አስቸኳይ ጉባዔውን አካሂዷል።
ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አሳዬ በላይነህ እና ደረበ አያሌው፤ በከተማ አስተዳደሩ የተያዙ እቅዶችን በመደገፍና ክትትል በማድረግ ለተፈፃሚነታቸው በትኩረት እንሰራለን ብለዋል።
የወልዲያ ከተማና አካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም በቅንጅት መሰራት እንዳለበት የምክር ቤቱ አባላት አስገንዝበዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ንጉስ ዝናቡ፤ በክረምቱ ህብረተሰቡንና አጠቃላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን ያሰተፉ የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።
በዚህም መሰረት ከ54ሺህ 300 በላይ ሰዎች የተሳተፉባቸው የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ፣ በትምህርት ቤቶች የቁሳቁስ ማሟላትና ምቹ የማድረግ ስራ፣ የደም ልገሳ እና ሌሎችም አገልገሎቶች ተከናውነዋል ብለዋል።
በክረምቱ የታየው ጥሩ ጅምርና መልካም ተሞክሮን በመቀመር በበጋ ወቅትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025