🔇Unmute
ወልዲያ፤ መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦ የወልዲያ ከተማና አካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት አባላት ገለጹ።
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር፣ 12ኛ ዓመት፣ 17ኛ አስቸኳይ ጉባዔውን አካሂዷል።
ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አሳዬ በላይነህ እና ደረበ አያሌው፤ በከተማ አስተዳደሩ የተያዙ እቅዶችን በመደገፍና ክትትል በማድረግ ለተፈፃሚነታቸው በትኩረት እንሰራለን ብለዋል።
የወልዲያ ከተማና አካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም በቅንጅት መሰራት እንዳለበት የምክር ቤቱ አባላት አስገንዝበዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ንጉስ ዝናቡ፤ በክረምቱ ህብረተሰቡንና አጠቃላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን ያሰተፉ የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።
በዚህም መሰረት ከ54ሺህ 300 በላይ ሰዎች የተሳተፉባቸው የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ፣ በትምህርት ቤቶች የቁሳቁስ ማሟላትና ምቹ የማድረግ ስራ፣ የደም ልገሳ እና ሌሎችም አገልገሎቶች ተከናውነዋል ብለዋል።
በክረምቱ የታየው ጥሩ ጅምርና መልካም ተሞክሮን በመቀመር በበጋ ወቅትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026