🔇Unmute
ወልዲያ፤ መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦ የወልዲያ ከተማና አካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት አባላት ገለጹ።
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር፣ 12ኛ ዓመት፣ 17ኛ አስቸኳይ ጉባዔውን አካሂዷል።
ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አሳዬ በላይነህ እና ደረበ አያሌው፤ በከተማ አስተዳደሩ የተያዙ እቅዶችን በመደገፍና ክትትል በማድረግ ለተፈፃሚነታቸው በትኩረት እንሰራለን ብለዋል።
የወልዲያ ከተማና አካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም በቅንጅት መሰራት እንዳለበት የምክር ቤቱ አባላት አስገንዝበዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ንጉስ ዝናቡ፤ በክረምቱ ህብረተሰቡንና አጠቃላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን ያሰተፉ የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።
በዚህም መሰረት ከ54ሺህ 300 በላይ ሰዎች የተሳተፉባቸው የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ፣ በትምህርት ቤቶች የቁሳቁስ ማሟላትና ምቹ የማድረግ ስራ፣ የደም ልገሳ እና ሌሎችም አገልገሎቶች ተከናውነዋል ብለዋል።
በክረምቱ የታየው ጥሩ ጅምርና መልካም ተሞክሮን በመቀመር በበጋ ወቅትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026