🔇Unmute
አዲስ አበባ፤መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦በክልሎቹ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡና ብልፅግናን እውን በሚያደርጉ የልማት ሥራዎች አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የጋምቤላና ሲዳማ ክልሎች ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች ገለፁ።
የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ጋትሉዋክ ሮን በክልሉ በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ለሚፈልጉ አካላት በርካታ አማራጮች መኖራቸውን ተናግረዋል።
በማዕድን ዘርፍ የሚታየውን ህገወጥ ተግባር በመቆጣጠርና ፍትሃዊ አሰራር በማስፈን ከክልሉ አልፎ እንደአገር የተሻለ ገቢ ማግኘት እንደሚቻል ገልፀዋል።
በክልሉ ለግብርና ምቹ የሆነ ሰፊ መሬት፣ የቁም እንስሳትና የዓሳ ሀብት በመኖሩ ያለውን ሀብት በመጠቀም፣ የግብይት ስርዓቱን በማሳለጥና የአገር ውስጥና ቀጣናዊ የንግድ ትስስርን በማጠናከር ገቢን ማሻሻል ይቻላል ብለዋል።
በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው በተለይም በሆቴል ልማት፣ መሬት አስተዳደርና ህገ ወጥ ኬላ ላይ የሚታዩ ችግሮችን በመቆጣጠር በክልሉ የሚሰበሰበውን ገቢ ለማሳደግ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ ከተረጂነት ለመውጣት የጀመረችውን ጉዞ ለማሳካት በክልሉ የተጀመረውን ልማት በማጠናከር የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልፀዋል።
የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ በየነ በራሳ በበኩላቸው፤ ክልሉ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በትምህርት ለትውልድ መርሃ ግብር በላቀ የህዝብ ተሳትፎ የትምህርት ቤቶች ገፅታ እየተቀየረ መምጣቱን አስታውቀዋል።
በጤና፣በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርና በእርሻ ልማት አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልፀዋል።
በክልሉ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፥ የግለሰቦችን ህይወት ለመቀየር የቤተሰብ ብልፅግና (አቴቴ ጅሬኛ) የተሰኘ መርሃ ግብር እየተተገበረ መሆኑን በአብነት ጠቅሰዋል።
በዚህም የክልሉን ሀብት በመጠቀም የክልሉን ብሎም የአገርን ብልፅግና እውን ለማድረግና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮቹ በክልላቸው በተያዘው ዓመት የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልፀው፤ ይህንንም ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
የገቢ ዘርፍ ሪፎርም የሀገር ብሎም የክልሎች የገቢ አሰባሰብ አፈፃፀም እድገት ለማስመዝገብ ማስቻሉን ገልጸዋል፡፡
በዘርፉ ያሉ ችግሮችን በቅንጅት በመፍታት የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026