🔇Unmute
አርባ ምንጭ ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡-ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከኃይል አቅርቦት ባለፈ በተፈጠረው የንጋት ሃይቅ የቱሪዝም ዘርፍ ሀገራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ፋይዳው የጎላ ነው ሲሉ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ።
ላለፉት 14 ዓመታት የተለያዩ ተግዳሮቶችን በመቋቋም በአትዮጵያውያን የተባበረ ክንድ ለምረቃ የበቃው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ ባለፈ ለቀጣናው ሀገራትም ፀጋ ሆኗል።
ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከኃይል አቅርቦት ባለፈ በተፈጠረው የንጋት ሃይቅ የቱሪዝም ዘርፍ ሀገራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ፋይዳው የጎላ ነው።
በተጨማሪም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሀገርን ብሎም የአፍሪካ አህጉርን በጎ ገጽታ በመገንባት ረገድም በጎ ሚና እንዳለውም አመልክተዋል።
ግድቡ በሀይል አቅርቦት ልማትን ለማፋጥን ካለው ጠቀሜታ ባለፈ በቱሪዝም ዘርፍ ሀገራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅና የቀጣናው ሀገራትን ለማስተሳሰር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የዓለምን ቀልብ የሚስቡ ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊና ባህላዊ የቱሪዝም ሀብቶች እንዳሏት ገልጸው፣ የሕዳሴው ግድብም ለቱሪዝም ዘርፉ ተጨማሪ አቅም መሆኑን ምሁራኑ አንስተዋል።
ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል መምህር ሄኖክ በቀለ (ዶ/ር) እንዳሉት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሃይል ከማመንጨት ባለፈየንጋት ሃይቅ የቱሪዝም ዘርፉን የሚያነቃቃ ነው።

ይህም ለሀገር የኢኮኖሚ ጥቅም እንደሚያስገኝ ጠቅሰው፤ የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ቀልብ በመሳብ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠርና የንግድ እንቅስቃሴን በማሳለጥ ረገድ ድርሻው ከፍተኛ መሆኑንም ተናግረዋል።
እንደ ሄኖክ (ዶ/ር) ገለጻ ግድቡ ከሀገር ባለፈ የአፍሪካ አህጉርን ገጽታ በመገንባት በኩል ጠቀሜታው የጎላ ነው።
ኢትዮጵያ የተለያዩ የቱሪዝም ሀብቶች እንዳሏት ገልጸው፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለዘርፉ መጠናከር ተጨማሪ አቅም እንደሚሆንም ተናግረዋል።
የህዳሴ ግድቡ ተገንብቶ መጠናቀቅ ከቱሪዝም ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የገለፁት ደግሞ በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህር አባይ ወርቁ ናቸው።

ግድቡ በአካባቢ ጥበቃ፣ በንግድ እንዲሁም ከጎረቤት ሃገራት ጋር የሚኖርን ትብብር ከማጠናከር አንፃር አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረውም መምህር አባይ አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025