የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮሪደር ልማት ሥራን የማስፋቱ ተግባር ይጠናከራል

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች የማስፋት ተግባር እንደሚጠናከር የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በአሶሳ ከተማ በሁለተኛው ዙር የ12 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ መጀመሩም ተገልጿል።

የቢሮው ኃላፊ ሙሐመድ አልማሂ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ በክልሉ የሚገኙ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ሳቢ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

በዚህም በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች ለማስፋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም የኮሪደር ልማት ሥራውን በባምባሲ፣ በግልገል በለስ እና በካማሽ ከተሞች ላይ ለማከናወን የዝግጅት ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ኃላፊው ተናግረዋል።

እንደ ኃላፊው ገለፃ፤ በአሶሳ ከተማ ሁለተኛው ዙር የ12 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ተጀምሯል።


የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ በሁሉም አቅጣጫዎች በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች እንደሚከናወን አስረድተዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራው የእግረኛ መንገድን፣ አረንጓዴ ቦታዎች እና የተለያዩ የመዝናኛ ማዕከላትን እንደሚያካትት ጠቅሰው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አስታውቀዋል።

ህብረተሰቡ በመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ያሳየውን ትብብር አሁንም አጠናክሮ እንዲቀጥልና ለከተማዋ ልማት የድርሻውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።

ከዚህ በፊት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ውበት የጨመረ እና ለነዋሪዎች ምቹ መደላድል የፈጠረ በመሆኑ በሁለተኛው ዙር የሚከናወነው የኮሪደር ልማት ተግባር የከተማዋን ገፅታ የበለጠ እንደሚቀይረውም ተናግረዋል።

በአሶሳ ከተማ በመጀመሪያው ዙር 9 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት መከናወኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026