የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮሪደር ልማት ሥራን የማስፋቱ ተግባር ይጠናከራል

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች የማስፋት ተግባር እንደሚጠናከር የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በአሶሳ ከተማ በሁለተኛው ዙር የ12 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ መጀመሩም ተገልጿል።

የቢሮው ኃላፊ ሙሐመድ አልማሂ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ በክልሉ የሚገኙ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ሳቢ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

በዚህም በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች ለማስፋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም የኮሪደር ልማት ሥራውን በባምባሲ፣ በግልገል በለስ እና በካማሽ ከተሞች ላይ ለማከናወን የዝግጅት ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ኃላፊው ተናግረዋል።

እንደ ኃላፊው ገለፃ፤ በአሶሳ ከተማ ሁለተኛው ዙር የ12 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ተጀምሯል።


የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ በሁሉም አቅጣጫዎች በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች እንደሚከናወን አስረድተዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራው የእግረኛ መንገድን፣ አረንጓዴ ቦታዎች እና የተለያዩ የመዝናኛ ማዕከላትን እንደሚያካትት ጠቅሰው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አስታውቀዋል።

ህብረተሰቡ በመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ያሳየውን ትብብር አሁንም አጠናክሮ እንዲቀጥልና ለከተማዋ ልማት የድርሻውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።

ከዚህ በፊት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ውበት የጨመረ እና ለነዋሪዎች ምቹ መደላድል የፈጠረ በመሆኑ በሁለተኛው ዙር የሚከናወነው የኮሪደር ልማት ተግባር የከተማዋን ገፅታ የበለጠ እንደሚቀይረውም ተናግረዋል።

በአሶሳ ከተማ በመጀመሪያው ዙር 9 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት መከናወኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026