🔇Unmute
አሶሳ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች የማስፋት ተግባር እንደሚጠናከር የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በአሶሳ ከተማ በሁለተኛው ዙር የ12 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ መጀመሩም ተገልጿል።
የቢሮው ኃላፊ ሙሐመድ አልማሂ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ በክልሉ የሚገኙ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ሳቢ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
በዚህም በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች ለማስፋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም የኮሪደር ልማት ሥራውን በባምባሲ፣ በግልገል በለስ እና በካማሽ ከተሞች ላይ ለማከናወን የዝግጅት ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ኃላፊው ተናግረዋል።
እንደ ኃላፊው ገለፃ፤ በአሶሳ ከተማ ሁለተኛው ዙር የ12 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ተጀምሯል።

የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ በሁሉም አቅጣጫዎች በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች እንደሚከናወን አስረድተዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው የእግረኛ መንገድን፣ አረንጓዴ ቦታዎች እና የተለያዩ የመዝናኛ ማዕከላትን እንደሚያካትት ጠቅሰው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አስታውቀዋል።
ህብረተሰቡ በመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ያሳየውን ትብብር አሁንም አጠናክሮ እንዲቀጥልና ለከተማዋ ልማት የድርሻውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።
ከዚህ በፊት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ውበት የጨመረ እና ለነዋሪዎች ምቹ መደላድል የፈጠረ በመሆኑ በሁለተኛው ዙር የሚከናወነው የኮሪደር ልማት ተግባር የከተማዋን ገፅታ የበለጠ እንደሚቀይረውም ተናግረዋል።
በአሶሳ ከተማ በመጀመሪያው ዙር 9 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት መከናወኑ ይታወቃል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026