የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮሪደር ልማት ሥራን የማስፋቱ ተግባር ይጠናከራል

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች የማስፋት ተግባር እንደሚጠናከር የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በአሶሳ ከተማ በሁለተኛው ዙር የ12 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ መጀመሩም ተገልጿል።

የቢሮው ኃላፊ ሙሐመድ አልማሂ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ በክልሉ የሚገኙ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ሳቢ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

በዚህም በአሶሳ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች ለማስፋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም የኮሪደር ልማት ሥራውን በባምባሲ፣ በግልገል በለስ እና በካማሽ ከተሞች ላይ ለማከናወን የዝግጅት ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ኃላፊው ተናግረዋል።

እንደ ኃላፊው ገለፃ፤ በአሶሳ ከተማ ሁለተኛው ዙር የ12 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ተጀምሯል።


የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ በሁሉም አቅጣጫዎች በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች እንደሚከናወን አስረድተዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራው የእግረኛ መንገድን፣ አረንጓዴ ቦታዎች እና የተለያዩ የመዝናኛ ማዕከላትን እንደሚያካትት ጠቅሰው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አስታውቀዋል።

ህብረተሰቡ በመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ያሳየውን ትብብር አሁንም አጠናክሮ እንዲቀጥልና ለከተማዋ ልማት የድርሻውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።

ከዚህ በፊት የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ውበት የጨመረ እና ለነዋሪዎች ምቹ መደላድል የፈጠረ በመሆኑ በሁለተኛው ዙር የሚከናወነው የኮሪደር ልማት ተግባር የከተማዋን ገፅታ የበለጠ እንደሚቀይረውም ተናግረዋል።

በአሶሳ ከተማ በመጀመሪያው ዙር 9 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት መከናወኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026