🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦በሩብ ዓመቱ ከወጪ ንግድ ከ2 ነጥብ 48 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም የግምገማ መድረክ ተካሂዷል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት በሩብ ዓመቱ በዋና ዋና ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል።
በዚህም በ2018 በጀት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከወጪ ንግድ ከ 2 ነጥብ 48 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።
የወጪ ንግድ አፈፃፀም ከፍተኛ መሻሻል የታየበት መሆኑን በማንሳት በሩብ ዓመቱ የተገኘው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 65 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል።
በሩብ ዓመቱ የተመዘገበው የ117 በመቶ የዕቅድ አፈፃፀም በበጀት ዓመቱ የታቀደውን 9 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ማሳካት እንደሚቻል ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል።
ሩብ ዓመቱ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የተቃረበችበት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን የጀመረችበት መሆኑንም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025