የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኩዌት ፈንድ የኢትዮጵያን ግዙፍ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች እንደሚደግፍ ገለጸ

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ የኩዌት ፈንድ ለኢትዮጵያ ግዙፍ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቋል።

የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(IMF) አመታዊ ስብሰባ ላይ በዋሺንግተን ዲሲ መካሄዱን ቀጥሏል።

በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በዓመታዊው ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

በውይይቱ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተዋል።

አቶ አህመድ ሽዴ ከውይይቱ ጎን ለጎን ከኩዌት ፈንድ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጀነራል ዋሊድ አል-ባሃር ጋር ተወያይተዋል።


ውይይቱ የኢትዮጵያ እና የኩዌት ፈንድ የረጅም ጊዜ አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው።

የኢትዮጵያ ወቅታዊ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሞች፣ ፈንዱ በኢትዮጵያ እየደገፋቸው ያሉ ፕሮጀክቶች፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የልማት የትኩረት መስኮችና እድሎች እንዲሁም ፈንዱ በኢትዮጵያ ያለውን ተሳትፎ ማሳደግ በሚችልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር ተደርጓል።

አቶ አህመድ ሽዴ በውይይቱ ወቅት የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ጥረቶች እና ቁልፍ የልማት መስኮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።

የእዳ ሽግሽግ ሂደት፣ የግሉ ዘርፍ ልማትና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ግንባታ በማሳያነት የጠቀሱት ሚኒስትሩ በእነዚህ መስኮች የፈንዱ ድጋፍ ቁልፍ መሆኑን አመልክተዋል።

ከሁለቱ ወገኖች አበይት የውይይት ጉዳዮች አንዱ የኢትዮጵያን አዲስ ዓለም አቀፍ ግዙፍ አየር ማረፊያ በፋይናንስ መደገፍ የሚቻልበት መንገድ ይገኝበታል።

የኩዌት ፈንድ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጀነራል ዋሊድ አል-ባሃር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ራዕይ እና የሪፎርም አጀንዳው ጅምር ስኬቶችን አድንቀዋል።

የኩዌት ፈንድ የኢትዮጵያን ልማት በተለይም ግዙፍ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችና ሌሎች ቁልፍ መስኮችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።

ዋሊድ በማደግ ላይ ለሚገኙ ሀገራት ለሚደረጉ የልማት ፋይናንስ ድጋፎችን ከሚያስተባብረው " አረብ ኮርድኔሽን ግሩፕ" ጋር ያለውን ግንኙነት ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅሰው ይህሞ የአረብ የፋይናንስ ተቋማት የጋራ ትብብር እንደሚያጎለብትና ሀብትን በተቀናጀ መልኩ ማሰብሰብ እንደሚያስችል ተናግረዋል።

ሁለቱ ወገኖች አጋርነታቸውን ለማጠናከር የተስማሙ ሲሆን የኩዌት ፈንድ ለኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊና ከፍተኛ አዎንታዊ ለውጥ ለሚያመጡ የልማት ፕሮጀክቶች የሚያደርገውን ድጋፍ የበለጠ እንደሚያጠናክር የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።

በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከዓመታዊ ስብሰባው ጎን ለጎን ከበርካታ የባለብዙ ወገን ድርጅቶችና ተቋማት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026