🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ የኩዌት ፈንድ ለኢትዮጵያ ግዙፍ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቋል።
የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(IMF) አመታዊ ስብሰባ ላይ በዋሺንግተን ዲሲ መካሄዱን ቀጥሏል።
በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በዓመታዊው ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
በውይይቱ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተዋል።
አቶ አህመድ ሽዴ ከውይይቱ ጎን ለጎን ከኩዌት ፈንድ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጀነራል ዋሊድ አል-ባሃር ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ የኢትዮጵያ እና የኩዌት ፈንድ የረጅም ጊዜ አጋርነት ማጠናከርን ያለመ ነው።
የኢትዮጵያ ወቅታዊ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሞች፣ ፈንዱ በኢትዮጵያ እየደገፋቸው ያሉ ፕሮጀክቶች፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የልማት የትኩረት መስኮችና እድሎች እንዲሁም ፈንዱ በኢትዮጵያ ያለውን ተሳትፎ ማሳደግ በሚችልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር ተደርጓል።
አቶ አህመድ ሽዴ በውይይቱ ወቅት የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ጥረቶች እና ቁልፍ የልማት መስኮች አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።
የእዳ ሽግሽግ ሂደት፣ የግሉ ዘርፍ ልማትና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ግንባታ በማሳያነት የጠቀሱት ሚኒስትሩ በእነዚህ መስኮች የፈንዱ ድጋፍ ቁልፍ መሆኑን አመልክተዋል።
ከሁለቱ ወገኖች አበይት የውይይት ጉዳዮች አንዱ የኢትዮጵያን አዲስ ዓለም አቀፍ ግዙፍ አየር ማረፊያ በፋይናንስ መደገፍ የሚቻልበት መንገድ ይገኝበታል።
የኩዌት ፈንድ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጀነራል ዋሊድ አል-ባሃር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ራዕይ እና የሪፎርም አጀንዳው ጅምር ስኬቶችን አድንቀዋል።
የኩዌት ፈንድ የኢትዮጵያን ልማት በተለይም ግዙፍ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችና ሌሎች ቁልፍ መስኮችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዋሊድ በማደግ ላይ ለሚገኙ ሀገራት ለሚደረጉ የልማት ፋይናንስ ድጋፎችን ከሚያስተባብረው " አረብ ኮርድኔሽን ግሩፕ" ጋር ያለውን ግንኙነት ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅሰው ይህሞ የአረብ የፋይናንስ ተቋማት የጋራ ትብብር እንደሚያጎለብትና ሀብትን በተቀናጀ መልኩ ማሰብሰብ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
ሁለቱ ወገኖች አጋርነታቸውን ለማጠናከር የተስማሙ ሲሆን የኩዌት ፈንድ ለኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊና ከፍተኛ አዎንታዊ ለውጥ ለሚያመጡ የልማት ፕሮጀክቶች የሚያደርገውን ድጋፍ የበለጠ እንደሚያጠናክር የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከዓመታዊ ስብሰባው ጎን ለጎን ከበርካታ የባለብዙ ወገን ድርጅቶችና ተቋማት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026