የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በሀዲያ ዞን  የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የዘርፉን ስኬቶች ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ በሀዲያ ዞን የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል በዘርፉ እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ፡፡

የዞኑ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል፡፡


በመምሪያው የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ መሰረት አበራ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በዞኑ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡


ለእንስሳት ጤና የሚሆን መኖ ከማዘጋጀት ጀምሮ ዝርያቸውን ለማሻሻል የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

በዘርፉ እየተከናወነ ባለው ዘመናዊ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ዮሐንስ በበኩላቸው በከተማው የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል ከወተት ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በዚህም ባለፈው ዓመት በተከናወነው የእንስሳት ዝርያ የማሻሻል ስራን 82 በመቶ ላይ ማድረስ መቻሉን ጠቅሰው፤ በዚህም የወተት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በተከናወነው ስራ አበረታች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡

በሆሳዕና ከተማ በሊች አምባ ቀበሌ በእንስሳት እርባታ ላይ የተሰማሩት አቶ ዳንኤል ብርሃኑ እና በከተማው የሄጦ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ግርማ ቲርካሶ፤ መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ በሰጠው ትኩረት የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ትግበራው ውጤታማ እያደረገን ነው ብለዋል፡፡


በመርሐ ግብሩ ላይ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና አርሶ አደሮች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026