የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በሀዲያ ዞን  የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የዘርፉን ስኬቶች ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ በሀዲያ ዞን የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል በዘርፉ እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ፡፡

የዞኑ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል፡፡


በመምሪያው የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ መሰረት አበራ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በዞኑ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡


ለእንስሳት ጤና የሚሆን መኖ ከማዘጋጀት ጀምሮ ዝርያቸውን ለማሻሻል የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

በዘርፉ እየተከናወነ ባለው ዘመናዊ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ዮሐንስ በበኩላቸው በከተማው የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል ከወተት ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በዚህም ባለፈው ዓመት በተከናወነው የእንስሳት ዝርያ የማሻሻል ስራን 82 በመቶ ላይ ማድረስ መቻሉን ጠቅሰው፤ በዚህም የወተት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በተከናወነው ስራ አበረታች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡

በሆሳዕና ከተማ በሊች አምባ ቀበሌ በእንስሳት እርባታ ላይ የተሰማሩት አቶ ዳንኤል ብርሃኑ እና በከተማው የሄጦ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ግርማ ቲርካሶ፤ መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ በሰጠው ትኩረት የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ትግበራው ውጤታማ እያደረገን ነው ብለዋል፡፡


በመርሐ ግብሩ ላይ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና አርሶ አደሮች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026