🔇Unmute
ሆሳዕና፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ በሀዲያ ዞን የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል በዘርፉ እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ፡፡
የዞኑ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል፡፡

በመምሪያው የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ መሰረት አበራ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በዞኑ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡

ለእንስሳት ጤና የሚሆን መኖ ከማዘጋጀት ጀምሮ ዝርያቸውን ለማሻሻል የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
በዘርፉ እየተከናወነ ባለው ዘመናዊ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ መርሃ ግብር ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል።
የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ዮሐንስ በበኩላቸው በከተማው የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል ከወተት ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህም ባለፈው ዓመት በተከናወነው የእንስሳት ዝርያ የማሻሻል ስራን 82 በመቶ ላይ ማድረስ መቻሉን ጠቅሰው፤ በዚህም የወተት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በተከናወነው ስራ አበረታች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል፡፡
በሆሳዕና ከተማ በሊች አምባ ቀበሌ በእንስሳት እርባታ ላይ የተሰማሩት አቶ ዳንኤል ብርሃኑ እና በከተማው የሄጦ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ግርማ ቲርካሶ፤ መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ በሰጠው ትኩረት የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ትግበራው ውጤታማ እያደረገን ነው ብለዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና አርሶ አደሮች ተገኝተዋል፡፡
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026