የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በማዘመን የዜጎችን የልማት ተጠቃሚነት የሚያሻሽል የገቢ አቅም እየተፈጠረ ነው

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በማዘመን የዜጎችን የልማት ተጠቃሚነት የሚያሻሽል የገቢ አቅም እየተፈጠረ እንደሚገኝ የክልሎች ገቢ ቢሮዎች ኃላፊዎች ገለጹ።

የኦሮሚያ፣ የአማራና የጋምቤላ ክልሎች የገቢ ቢሮዎች ኃላፊዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዕቅድ የተቀመጠውን ገቢ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ተስፋዬ ቱሉ፤ ዘመናዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት በመዘርጋት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከሚያመነጨው ሃብት የሚሰበሰበው ገቢ ዕድገት እያስመዘገበ ነው ብለዋል።

ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ እያደገ የመጣው ግንዛቤ፣ የአሰራር መሻሻያዎችና የክልሉ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴም የታክስ መሰረትን በማስፋት ለገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱ ትልቅ ዕድል እየፈጠሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ክብረት ማህሙድ፤ የግብር ክፍያ አገልግሎትን የሚያሳልጡ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች የተገልጋዮችን እንግልትና ያልተገባ ወጪ በመቀነስ ጉልህ ጠቀሜታ እያበረከቱ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

ግብር ከፋዮችም የሚጠበቅባቸውን ታክስ በታማኝነትና በቅንነት በመክፈል ለሀገር ልማትና ዕድገት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የጋምቤላ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቸንኮ ዴቪድ፤ የገቢ አቅምን በማሳደግ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

በ2018 በጀት ዓመትም የገቢ ግብርን ማሻሻል የሚያስችል ግንዛቤ የመፍጠርና የዲጂታል አገልግሎት ሥርዓት የመዘርጋት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም የኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ መነቃቃትን በማሻሻል ዕድገትን የሚያሳልጥ የታክስ አስተዳደር ሥርዓት በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026