የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በማዘመን የዜጎችን የልማት ተጠቃሚነት የሚያሻሽል የገቢ አቅም እየተፈጠረ ነው

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በማዘመን የዜጎችን የልማት ተጠቃሚነት የሚያሻሽል የገቢ አቅም እየተፈጠረ እንደሚገኝ የክልሎች ገቢ ቢሮዎች ኃላፊዎች ገለጹ።

የኦሮሚያ፣ የአማራና የጋምቤላ ክልሎች የገቢ ቢሮዎች ኃላፊዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዕቅድ የተቀመጠውን ገቢ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ተስፋዬ ቱሉ፤ ዘመናዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት በመዘርጋት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከሚያመነጨው ሃብት የሚሰበሰበው ገቢ ዕድገት እያስመዘገበ ነው ብለዋል።

ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ እያደገ የመጣው ግንዛቤ፣ የአሰራር መሻሻያዎችና የክልሉ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴም የታክስ መሰረትን በማስፋት ለገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱ ትልቅ ዕድል እየፈጠሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ክብረት ማህሙድ፤ የግብር ክፍያ አገልግሎትን የሚያሳልጡ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች የተገልጋዮችን እንግልትና ያልተገባ ወጪ በመቀነስ ጉልህ ጠቀሜታ እያበረከቱ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

ግብር ከፋዮችም የሚጠበቅባቸውን ታክስ በታማኝነትና በቅንነት በመክፈል ለሀገር ልማትና ዕድገት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የጋምቤላ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቸንኮ ዴቪድ፤ የገቢ አቅምን በማሳደግ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

በ2018 በጀት ዓመትም የገቢ ግብርን ማሻሻል የሚያስችል ግንዛቤ የመፍጠርና የዲጂታል አገልግሎት ሥርዓት የመዘርጋት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም የኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ መነቃቃትን በማሻሻል ዕድገትን የሚያሳልጥ የታክስ አስተዳደር ሥርዓት በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026