🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በማዘመን የዜጎችን የልማት ተጠቃሚነት የሚያሻሽል የገቢ አቅም እየተፈጠረ እንደሚገኝ የክልሎች ገቢ ቢሮዎች ኃላፊዎች ገለጹ።
የኦሮሚያ፣ የአማራና የጋምቤላ ክልሎች የገቢ ቢሮዎች ኃላፊዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዕቅድ የተቀመጠውን ገቢ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የኦሮሚያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ተስፋዬ ቱሉ፤ ዘመናዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት በመዘርጋት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከሚያመነጨው ሃብት የሚሰበሰበው ገቢ ዕድገት እያስመዘገበ ነው ብለዋል።
ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ እያደገ የመጣው ግንዛቤ፣ የአሰራር መሻሻያዎችና የክልሉ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴም የታክስ መሰረትን በማስፋት ለገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱ ትልቅ ዕድል እየፈጠሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ክብረት ማህሙድ፤ የግብር ክፍያ አገልግሎትን የሚያሳልጡ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች የተገልጋዮችን እንግልትና ያልተገባ ወጪ በመቀነስ ጉልህ ጠቀሜታ እያበረከቱ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ግብር ከፋዮችም የሚጠበቅባቸውን ታክስ በታማኝነትና በቅንነት በመክፈል ለሀገር ልማትና ዕድገት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የጋምቤላ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቸንኮ ዴቪድ፤ የገቢ አቅምን በማሳደግ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
በ2018 በጀት ዓመትም የገቢ ግብርን ማሻሻል የሚያስችል ግንዛቤ የመፍጠርና የዲጂታል አገልግሎት ሥርዓት የመዘርጋት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም የኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ መነቃቃትን በማሻሻል ዕድገትን የሚያሳልጥ የታክስ አስተዳደር ሥርዓት በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026