የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአፍሪካ ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ ክህሎት ማሳደግ ይገባል

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ዘላቂና ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ ክህሎት ማሳደግ እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ።

ከጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 2ኛው የአፍሪካ የክህሎት ሳምንት ዛሬ ተጠናቋል።


የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) መርሃ ግብሩ፣ በአፍሪካ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠናን ጥራት ለመጠበቅና ተደራሽነቱን ለማስፋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ምርጥ ተሞክሮ ያካፈለችበት እና ከሌሎች ልምድ የወሰደችበት ስኬታማ መድረክ እንደነበርም ገልጸዋል።

የአፍሪካ መጻዒ እድል የሚወሰነው በወጣቶች ላይ በምንሰራው ሁሉን አቀፍ የክህሎት ልማት ስራ ልክ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

በአፍሪካ ዘላቂና ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደግ እንደሚገባም አመላክተዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለሰው ሀብት ልማት ስራ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች እንደምትገኝ ጠቁመው፤ በቀጣይም ከአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ጋር በማስተሳሰር አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታውቀዋል።


በመድረኩ ማጠቃለያም የአፍሪካ አገራት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሀብት ለማፍራት በጋራ የሚሰሩበት አቅጣጫ መቀመጡንም አመላክተዋል።

በአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጋስፓርድ ዳንያንክምቦና በበኩላቸው፤ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት የእድገት ማሳለጫ ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በመሆኑም የአፍሪካ አገራት በአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳ መሰረት ቅንጅት በመፍጠር ዘርፉን በማሳደግ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

የዛሬ የአፍሪካ ወጣቶች ነገን ፈጠራ በታከለበት ሁኔታ መምራትና ለውጥ የማምጣት ሃላፊነት እንደተጣለባቸው አንስተው፤በዚህ ሒደት ውስጥ ከጎናቸው እንደሚሆኑ አረጋግጠዋል፡፡

ከኢኳቶሪያል ጊኒ የመጡ የመድረኩ ተሳታፊ ዮላንዳ አሱሙ በበኩላቸው፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የክህሎት ሳምንት በርካታ ልምዶችን የተለዋወጥንበት ነበር ብለዋል፡፡


የአፍሪካ ሁለተኛው ክህሎት ሳምንት እጅግ አስተማሪና ትልቅ ግንዛቤ የወሰድንበት ሆኖ አልፏል ያለው ደግሞ ከሴኔጋል የመጣው ወጣት ደቪድ ሞዓድ ነው፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026