🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ዘላቂና ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ ክህሎት ማሳደግ እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ።
ከጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 2ኛው የአፍሪካ የክህሎት ሳምንት ዛሬ ተጠናቋል።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) መርሃ ግብሩ፣ በአፍሪካ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠናን ጥራት ለመጠበቅና ተደራሽነቱን ለማስፋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ምርጥ ተሞክሮ ያካፈለችበት እና ከሌሎች ልምድ የወሰደችበት ስኬታማ መድረክ እንደነበርም ገልጸዋል።
የአፍሪካ መጻዒ እድል የሚወሰነው በወጣቶች ላይ በምንሰራው ሁሉን አቀፍ የክህሎት ልማት ስራ ልክ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
በአፍሪካ ዘላቂና ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደግ እንደሚገባም አመላክተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለሰው ሀብት ልማት ስራ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች እንደምትገኝ ጠቁመው፤ በቀጣይም ከአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ጋር በማስተሳሰር አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታውቀዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያም የአፍሪካ አገራት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሀብት ለማፍራት በጋራ የሚሰሩበት አቅጣጫ መቀመጡንም አመላክተዋል።
በአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጋስፓርድ ዳንያንክምቦና በበኩላቸው፤ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት የእድገት ማሳለጫ ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም የአፍሪካ አገራት በአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳ መሰረት ቅንጅት በመፍጠር ዘርፉን በማሳደግ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡
የዛሬ የአፍሪካ ወጣቶች ነገን ፈጠራ በታከለበት ሁኔታ መምራትና ለውጥ የማምጣት ሃላፊነት እንደተጣለባቸው አንስተው፤በዚህ ሒደት ውስጥ ከጎናቸው እንደሚሆኑ አረጋግጠዋል፡፡
ከኢኳቶሪያል ጊኒ የመጡ የመድረኩ ተሳታፊ ዮላንዳ አሱሙ በበኩላቸው፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የክህሎት ሳምንት በርካታ ልምዶችን የተለዋወጥንበት ነበር ብለዋል፡፡

የአፍሪካ ሁለተኛው ክህሎት ሳምንት እጅግ አስተማሪና ትልቅ ግንዛቤ የወሰድንበት ሆኖ አልፏል ያለው ደግሞ ከሴኔጋል የመጣው ወጣት ደቪድ ሞዓድ ነው፡፡

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026