የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ሕገ ወጥ ድርጊት ሲፈጽሙ በተገኙ የነዳጅ ማደያዎች ላይ ርምጃ ተወሰደ

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በ2018 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከነዳጅ ሽያጭ እና ማከፋፈል ሂደት ጋር በተያያዘ ሕገ ወጥ ድርጊት በፈጸሙ ማደያዎች ላይ ርምጃ መወሰዱን የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታወቀ።

በዚህም መሠረት፤ ዲጂታል ሽያጫቸው ከ50 በመቶ በታች በሆኑ 354 የነዳጅ ማደያዎች ላይ በአዋጁ መሠረት ርምጃ መወሰዱን የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ በቀለች ኩማ ለኢዜአ ተናግረዋል።

በተመሳሳይ ዲጂታል ሽያጫቸው ዝቅተኛ በሆኑ ሥድስት የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች ላይ በአዋጁ መሠረት ለሁለት ወራት የነዳጅ ጭነት እንዳይደረግላቸው መደረጉንም ጠቅሰዋል።

በሌላ በኩል የዲጂታል ሽያጫቸው መጠነኛ በሆኑ ሰባት ኩባንያዎች ላይ በአዋጁ መሰረት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን ነው የጠቀሱት።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል አንድ ማደያ ነዳጅ በበርሜል በመቅዳት የጥቁር ገበያ ሽያጭ ለማከናወን ሲንቀሳቀስ በመያዙ ለሥድስት ወራት ከነዳጅ ትስስር መታገዱንም ገልጸዋል።

በሌላ በኩል መዳረሻው አዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ በሚገኝ ማደያ የነበረ አውቶ ቦቴ መዳረሻውን በመቀየር ወደ ሌላ ከተማ በመጓዙ ለሥድስት ወራት ከነዳጅ ትስስር እንዲታገድ መደረጉን ተናግረዋል።

በተመሳሳይ በዲላ ከተማ የሚገኝ አንድ ማደያም መንግሥት ካወጣው ዋጋ በላይ በመሸጡ የነዳጅ አቅርቦት እንዳያገኝ በሲስተም ሎክ መደረጉን ነው ያረጋገጡት።

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን የነዳጅ አቅርቦት፣ ሥርጭትና ግብይት ቁጥጥር ሥርዓቱ ፈጣን፣ አስተማማኝና ጥራት ያለው እንዲሆን በቴክኖሎጂ የታገዙ አሠራሮችን ማጠናከሩንም አስታውቋል።

ሁሉም የነዳጅ አከፋፋዮችና ማደያዎች ህግን ተከትለው መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026