🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በ2018 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከነዳጅ ሽያጭ እና ማከፋፈል ሂደት ጋር በተያያዘ ሕገ ወጥ ድርጊት በፈጸሙ ማደያዎች ላይ ርምጃ መወሰዱን የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታወቀ።
በዚህም መሠረት፤ ዲጂታል ሽያጫቸው ከ50 በመቶ በታች በሆኑ 354 የነዳጅ ማደያዎች ላይ በአዋጁ መሠረት ርምጃ መወሰዱን የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ በቀለች ኩማ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በተመሳሳይ ዲጂታል ሽያጫቸው ዝቅተኛ በሆኑ ሥድስት የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች ላይ በአዋጁ መሠረት ለሁለት ወራት የነዳጅ ጭነት እንዳይደረግላቸው መደረጉንም ጠቅሰዋል።
በሌላ በኩል የዲጂታል ሽያጫቸው መጠነኛ በሆኑ ሰባት ኩባንያዎች ላይ በአዋጁ መሰረት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን ነው የጠቀሱት።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል አንድ ማደያ ነዳጅ በበርሜል በመቅዳት የጥቁር ገበያ ሽያጭ ለማከናወን ሲንቀሳቀስ በመያዙ ለሥድስት ወራት ከነዳጅ ትስስር መታገዱንም ገልጸዋል።
በሌላ በኩል መዳረሻው አዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ በሚገኝ ማደያ የነበረ አውቶ ቦቴ መዳረሻውን በመቀየር ወደ ሌላ ከተማ በመጓዙ ለሥድስት ወራት ከነዳጅ ትስስር እንዲታገድ መደረጉን ተናግረዋል።
በተመሳሳይ በዲላ ከተማ የሚገኝ አንድ ማደያም መንግሥት ካወጣው ዋጋ በላይ በመሸጡ የነዳጅ አቅርቦት እንዳያገኝ በሲስተም ሎክ መደረጉን ነው ያረጋገጡት።
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን የነዳጅ አቅርቦት፣ ሥርጭትና ግብይት ቁጥጥር ሥርዓቱ ፈጣን፣ አስተማማኝና ጥራት ያለው እንዲሆን በቴክኖሎጂ የታገዙ አሠራሮችን ማጠናከሩንም አስታውቋል።
ሁሉም የነዳጅ አከፋፋዮችና ማደያዎች ህግን ተከትለው መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026