የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለማልማት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ነው

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ ጥራቱን የጠበቀ ቡና በማልማት ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የኦሮሚያና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች ገለጹ።

በግብርናው ዘርፍ ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ከሚገኙ ምርቶች መካከል ቡና ተጠቃሽ ነው።

ኢትዮጵያም ቡናን ወደ ውጭ በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ አቅም እየፈጠረ እንደሚገኝ ይታወቃል።

የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊ እና የቡናና ፍራፍሬ ልማት ዘርፍ ሃላፊ መሀመድ ሳኒ በክልሉ ቡናን የማልማት ስራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ቡና ለሀገሪቱ ልማት የሚኖረውን አበርክቶ በአግባቡ ለመጠቀም የቡና ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ያረጁ የቡና ተክሎችን በአዲስ በመተካት፣ የቡና አመራረትን የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ በማዋል፣ ተመራጭ የሆኑ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ማከፋፈልን ጨምሮ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቡናና ሻይ ባለስልጣን የቡናና ሻይ ልማት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ካሳሁን ታዬ፤ በክልሉ በቡና ዘርፍ የሚሰሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ለቡና አመራረት ሂደት ተገቢውን እንክብካቤ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት ውስጥ ምርት የማይሰጡ የቡና ተክሎችን በሌላ የመተካት፣ ምርጥ የሆኑ የቡና ዝርያዎችን ከምርምር ተቋማት ጋር ለአርሶ አደሮች እንዲደርስ የማድረግ ተግባር መጠናከሩን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በስፋት የቡና ችግኞች እንዲፈሉ በማድረግ ለተጠቃሚዎች እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026