የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለማልማት የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ነው

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ ጥራቱን የጠበቀ ቡና በማልማት ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የኦሮሚያና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች ገለጹ።

በግብርናው ዘርፍ ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ከሚገኙ ምርቶች መካከል ቡና ተጠቃሽ ነው።

ኢትዮጵያም ቡናን ወደ ውጭ በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ አቅም እየፈጠረ እንደሚገኝ ይታወቃል።

የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊ እና የቡናና ፍራፍሬ ልማት ዘርፍ ሃላፊ መሀመድ ሳኒ በክልሉ ቡናን የማልማት ስራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ቡና ለሀገሪቱ ልማት የሚኖረውን አበርክቶ በአግባቡ ለመጠቀም የቡና ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ያረጁ የቡና ተክሎችን በአዲስ በመተካት፣ የቡና አመራረትን የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ በማዋል፣ ተመራጭ የሆኑ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ማከፋፈልን ጨምሮ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቡናና ሻይ ባለስልጣን የቡናና ሻይ ልማት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ካሳሁን ታዬ፤ በክልሉ በቡና ዘርፍ የሚሰሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ለቡና አመራረት ሂደት ተገቢውን እንክብካቤ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት ውስጥ ምርት የማይሰጡ የቡና ተክሎችን በሌላ የመተካት፣ ምርጥ የሆኑ የቡና ዝርያዎችን ከምርምር ተቋማት ጋር ለአርሶ አደሮች እንዲደርስ የማድረግ ተግባር መጠናከሩን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በስፋት የቡና ችግኞች እንዲፈሉ በማድረግ ለተጠቃሚዎች እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026