🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 15/2018(ኢዜአ):- በክህሎት መር የሥራ ዕድል የተፈጠረው ምቹ መደላድል አማራጭ የስራ እድሎች መስፋታቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዜጎችን የስራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ የስራ መስኮች በአማራጭነት እየተስፋፉ ናቸው።
ግብርና፣ ቱሪዝም፣ የኮንስትራክሽን እና ሌሎች መስኮች ለስራ እድል ፈጠራ አቅም እየፈጠሩ መሆናቸውን ነው ያነሱት።

እነዚህን የስራ ዕድሎች በመጠቀም የሀገርን ምጣኔ ሃብታዊ እድገት ማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው፤ በዚህም ገበያው የሚፈልገውን የሰው ሀይል እና ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ማጎልበት እንደሚጠይቅ ተናግረዋል።
በዚህም ዜጎች ያካበቱትን ክህሎት ወደ ስራ መቀየር እንዳለባቸው አመልክተው፤ የዲጂታል አማራጮች እንዲሁም ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው ውጤታማ የሚሆኑበትን ምቹ መደላድል ፈጥሯል ብለዋል።

ዜጎች በክህሎት መር የሥራ ዕድል የተፈጠረውን መልካም ሁኔታ በመጠቀም ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባቸው ጠቁመዋል።
የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር ) በበኩላቸው፤ ኢንስቲትዩቱ በክህሎትና በፈጠራ ሥራ የተካነ የሰው ሀይል በማፍራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ኢኒስቲትዩቱ የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ 11 አዳዲስ የስልጠና ፕሮግራሞችን ቀርጾ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን አስታውቀዋል።
ከስልጠና ፕሮግራሞቹም መካከል አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ሳይበር ሴክዩሪቲ፣ ባዮ ሜዲካል ቴክኖሎጂ፣ ፕላስቲክ ቴክኖሎጂ እና ኢንቴሪየር ዲዛይንን ለማሳያነት አንስተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም፤ በየክልሎች ያሉ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በየአካባቢያቸው ያሉ ጸጋዎችን ታሳቢ ያደረጉ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አይነቶች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ለማስቻል ኢንስቲትዩቱ የዘርፉ ተዋናዮች አቅም ግንባታ ተግባር እያከናወነ ነው።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026