የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የኢንቨስትመንት ትስስር ሊጠናከር ይገባል

Oct 27, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 15/2018(ኢዜአ):-በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የኢንቨስትመንት ትስስር ሊጠናከር እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ።

11ኛው ጣና ፎረም በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ሲሆን መሪዎች፣የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ልዩ መልዕክተኞች ምሁራንና ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።


በፎረሙ ላይ አፍሪካ በኢኮኖሚ፣ በሰላምና ደህንነት፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች የሚገጥሙ ችግሮችና መፍትሄዎች ላይ ትኩረት ያደረገ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በፓናል ውይይቱ ላይ እንዳሉት፤የአፍሪካ ሀገራት በራስ አቅም የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ሊያመቻቹ ይገባል።

ወጣቶች እና ሴቶች እንዲሁም ቴክኖሎጂ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ መበልጸግ አቀጣጣይ ሞተር እንዲሆኑ ማድረግ ይገባል ያሉት ሚኒስትሩ፤ መሰረተ ልማት ግንባታዎች ትኩረት ይፈልጋሉ ብለዋል።

ከኢንቨስትመንት አኳያም በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የኢንቨስትመንት ትስስር ሊጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል።


በአፍሪካ ያሉ ሥራ ፈጣሪዎች እና ቢዝነስ ተቋማት ኢንቨስት አድረገው አህጉራዊ የኢኮኖሚ ውህደት እንዲፋጠን ምቹ ሁኔታ የመፍጠር ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ኢንቨስት በማድረግ የሥራ ዕድል በመፍጠር ቀጣናዊ ትስስር እንዲጠናከር አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል።

የኬኒያ ቴሌኮም ኦፕሬተሮችም በኢትዮጵያ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን እና ናይጄሪያዊው ባለኃብት አሊኮ ዳንጎቴም በኢትዮጵያ ግዙፍ የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ፕሮጀክት መጀመሩን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በአፍሪካ ውስጥ የሚደረጉ መሰል የኢኮኖሚ ትስስሮች ለአፍሪካ ብልጽግናና ሉዓላዊነት መረጋገጥ ትልቅ እርምጃ መሆኑንም ነው ያስረዱት።

የቀድሞ የሞዛምቢክ ፕሬዝዳንት ጆአኪም ቺሳኖ በበኩላቸው፤ በአፍሪካ አገራት መካከል ግንኙነት ቢኖርም በበቂ ደረጃ ተሳስረዋል ማለት እንደማይቻል ተናግረዋል።


ግንኙነቱ መተማመን ላይ የተመሰረተ ሊሆን እንደሚገባ ጠቅሰው፤ በጋራ ጉዳዮች ላይ መተማመንን ማጽናት ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

የማላዊ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆይሴ ባንዳ (ዶ/ር) እንዳሉት፤አፍሪካ ለመበልጸግ የሚያስችል የተፈጥሮ ጸጋ ቢኖራትም ኃብቱን አልምቶ መጠቀም ላይ ግን ውስንነቶች መኖራቸውን ገልጸዋል።


ያሉ ዕድሎችን በመጠቀም ለተተኪው ትውልድ ሥራ መፍጠር እንደሚገባ ጠቁመው፤ ሴቶችን ማሳተፍም የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ቁልፍ አጀንዳ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026